የኢትዮጵያን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ውድድር የሚከፍት ሕግ በፓርላማ ጸደቀ የኢትዮጵያ ፓርላማ የምስራቅ አፍሪካዊቷን ሀገር የባንክ ዘርፍ ለውጭ ውድድር ክፍት የሚያደርገውን ሕግ ማክሰኞ እለት ያጸደቀ ሲሆን፤ መንግሥት የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ለሚያደረገው ሰፊ ጥረት ቁልፍ እርምጃ ነው። እርምጃው የውጭ ባንኮች ተቀጠላ ኩባንያዎች፣ ቅርንጫፎች ወይም ወኪል ቢሮዎችን እንዲያቋቁሙ እና በሀገር ውስጥ ባንኮች 40% የባለቤትነት ድርሻ እንዲኖራቸው ያስችላል። ይህም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተጀመረው መንግሥት መር ኢኮኖሚውን ነጻ የማድረግ ሂደት ትልቁ አካል ነው። ፓርላማው ህጉን በአብላጫ ድምጽ ቢያፀድቅም፤ አንዳንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት በሀገር ውስጥ ባንኮች ላይ ሊፈጠር የሚችለውን ተፅዕኖ በማንሳት ስጋታቸውን ገልጸዋል። የማዕከላዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ግን ፉክክር መኖሩ የኢትዮጵያ ባንኮችን ያጠናክራል ሲሉ ተከራክረዋል። ማሻሻያው ኢትዮጵያ በቅርቡ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ድጋፍ ማግኘቷን እና የብር መገበበያዋን ነጻ ማድረጓን ተከትሎ የመጣ ነው። በወለድ ተመን ላይ የተመሰረተ የገንዘብ ፖሊሲ ተግባራዊ ማድረግ የማሻሻያው አንዱ አካል ነው።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የኢትዮጵያን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ውድድር የሚከፍት ሕግ በፓርላማ ጸደቀ
የኢትዮጵያን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ውድድር የሚከፍት ሕግ በፓርላማ ጸደቀ
Sputnik አፍሪካ
የኢትዮጵያን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ውድድር የሚከፍት ሕግ በፓርላማ ጸደቀ የኢትዮጵያ ፓርላማ የምስራቅ አፍሪካዊቷን ሀገር የባንክ ዘርፍ ለውጭ ውድድር ክፍት የሚያደርገውን ሕግ ማክሰኞ እለት ያጸደቀ ሲሆን፤ መንግሥት የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ... 18.12.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-12-18T11:50+0300
2024-12-18T11:50+0300
2024-12-18T12:04+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий