ሞቷል ተብሎ በአስከሬን ክፍል ውስጥ ለአንድ ቀን የቆየ የጋዛ ሕጻን ተአምራዊ በሆነ መንገድ ተረፈ እስራኤል በጋዛ የስደተኞች ካምፕ ላይ ባካሄደችው የአየር ጥቃት ሞሐመድ አል-ዳላሳህ በስህተት ሞቷል ተብሎ ከሌሎች ተጎጂዎች ጋር ወደ አስከሬን ክፍል ተልኳል። አጎቱ የህይወት ምልክቶችን ከማየቱ በፊት 24 ሰዓታትን በአስክሬን ክፍሉ ውስጥ አሳልፏል። በፍጥነት ወደ ሆስፒታል የተወሰደው ሞሐመድ ከ15 ቀን ኮማ በኋላ ሊነቃ ችሏል። "ሞሐመድ በህይወት እንዳለ ሲታወቅ ችግሬን ሁሉ ረሳሁ፤ ምክንያቱም ከቤተሰቦቼ የተረፈ ሰው አግኝቻለሁ" ሲል አጎቱ ለስፑትኒክ ተናግሯል። ሕጻኑ ከባድ የጭንቅላት ጉዳት፣ የራስ ቅል ስብራት፣ አንድ ጆሮውን እንዳጣ እና እግሩ ላይ ጉዳት እንደደረሰበት አጎቱ ገልጿል። "በሰራተኞች እና በመሳሪያዎች እጥረት፣ ከጥቃተት በኋላ በሚፈጠር መጨናነቅ ምክንያት ይዋል ይደር እንጂ አንዳንድ ስህተቶች መከሰታቸው የማይቀር ነው" ብለዋል ዶክተር አህድ ኻላፍ። በተጣለው እገዳ ምክንያት ከባድ የሕክምና ባለሙያዎች እና መሳሪያዎች እጥረት ሁኔታውን እንዳባባሰ ዶክተሩ ተናግረዋል። ተግዳሮቶቹን ለመቅረፍ ለህክምና አቅርቦቶች እና የኤሌክትሪክ እጥረት መፍትሄ መስጠትን ጨምሮ የውጭ እርዳታ እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል። "እሱ (ሞሐመድ አል-ደአላህ) ሁሉንም ነገር ያስታውሳል። የሮኬት ድምፅ ሲሰማ መንቀጥቀጥ ይጀምራል። 'አለሁልህ፣ ምንም አትሆንም' ስለው ብቻ ነው እንቅልፍ የሚወስደው። ይህን የተረገመ ጦርነት አቁሙ። ሰዎች ወደ ቤታቸው ይመለሱበት" ሲል የሕጻኑ አጎት ተናግሯል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ሞቷል ተብሎ በአስከሬን ክፍል ውስጥ ለአንድ ቀን የቆየ የጋዛ ሕጻን ተአምራዊ በሆነ መንገድ ተረፈ
ሞቷል ተብሎ በአስከሬን ክፍል ውስጥ ለአንድ ቀን የቆየ የጋዛ ሕጻን ተአምራዊ በሆነ መንገድ ተረፈ
Sputnik አፍሪካ
ሞቷል ተብሎ በአስከሬን ክፍል ውስጥ ለአንድ ቀን የቆየ የጋዛ ሕጻን ተአምራዊ በሆነ መንገድ ተረፈ እስራኤል በጋዛ የስደተኞች ካምፕ ላይ ባካሄደችው የአየር ጥቃት ሞሐመድ አል-ዳላሳህ በስህተት ሞቷል ተብሎ ከሌሎች ተጎጂዎች ጋር ወደ አስከሬን ክፍል... 17.12.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-12-17T18:24+0300
2024-12-17T18:24+0300
2024-12-17T18:44+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
ሞቷል ተብሎ በአስከሬን ክፍል ውስጥ ለአንድ ቀን የቆየ የጋዛ ሕጻን ተአምራዊ በሆነ መንገድ ተረፈ
18:24 17.12.2024 (የተሻሻለ: 18:44 17.12.2024)
ሰብስክራይብ