ባሻር አል-አሳድ ሶሪያን ለቀው የወጡት "የመጨረሻዎቹ የሰራዊቱ ይዞታዎች ሲገረሰሱ ነው" ሲሉ ተናገሩ

ሰብስክራይብ
ባሻር አል-አሳድ ሶሪያን ለቀው የወጡት "የመጨረሻዎቹ የሰራዊቱ ይዞታዎች ሲገረሰሱ ነው" ሲሉ ተናገሩ አል-አሳድ ታጣቂዎች ደማስቆን ከተቆጣጠሩ በኋላ በሰጡት የመጀመሪያ መግለጫ ከሶሪያ የመውጣት እቅድ እንዳልነበራቸው ተናግረዋል። በቀድሞው የሶሪያ ፕሬዝዳንት የተነሱ ተጨማሪ ቁልፍ መግለጫዎች፦ 🟠 "አሸባሪዎች" ስልጣን ከተቆጣጠሩ በኋላ ፕሬዝዳንቱ በሀገር ውስጥ መቆየቱ አስፈላጊ አልነበረም። 🟠 አል-አሳድ ወደ ሩሲያ የሄዱት ከጦር ኃይሉ መውደቅ እና የመንግሥት ተቋማት መፈራረስ በኋላ ነው። 🟠 ሞስኮ የቀድሞው የሶሪያ መሪ ከደማስቆ ከሸሹ በኋላ ካረፉበት የሂሚም ጦር ሰፈር ለቃ ለመውጣት ጥያቄ አቅርባለች። 🟠 አል-አሳድ ስልጣን ለመልቀቅ ወይም ጥገኝነት ለመጠየቅ አስበው አያውቁም። 🟠 የቀድሞው የሶሪያ ፕሬዝዳንት በጦር ኃይሉም ሆነ በሶሪያ ህዝብ ተስፋ እንደማይቆርጡ እና ሶሪያ እንደገና ነፃ እና በራሷ የምትመራ እንደምትሆን ተስፋቸውን ገልጸዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0