የቀድሞው የሞሪሸስ ማዕከላዊ ባንክ ገዥ በማጭበርበር ወንጀል ምርመራ ተከፈተባቸው የሞሪሸስ ፖሊስ በአሁኑ ጊዜ ከሀገር ውጭ ናቸው የተባሉት የቀድሞ የማዕከላዊ ባንክ ገዥ ሃርቬሽ ኩማር ሴጎላም ላይ የእስር ማዘዣ አውጥቷል። የእስር ማዘዣው የገንዘብ ብዝበዛን አስመልክቶ የተከፈተው ምርመራ አካል ነው። የክሱ ዝርዝር ጉዳዮች አልተገለፁም። በቅርቡ በፓርላማ ይፋ የተደረገ ሪፖርት የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ኢኮኖሚያዊ ተፅእኖ ለመቋቋም በ2020 የተቋቋመውን የሞሪሸስ ኢንቨስትመንት ኮርፖሬሽን ለመደገፍ፤ በሕገ-ወጥ መንገድ ገንዘብ አትሟል ሲል የሞሪሸስ ማዕከላዊ ባንክ ላይ ክስ አቅርቧል። ባንኩ ይፋ የሆነውን የውጭ ምንዛሪ ክምችት ከመጠቀም ይልቅ፤ ገንዘብ በማተሙ ምክንያት በገንዘብ ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ለዋጋ ንረትና ለሀገሪቱ መገበያያ አለመረጋጋት አስተዋጽኦ አድርጓል ተብሏል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የቀድሞው የሞሪሸስ ማዕከላዊ ባንክ ገዥ በማጭበርበር ወንጀል ምርመራ ተከፈተባቸው
የቀድሞው የሞሪሸስ ማዕከላዊ ባንክ ገዥ በማጭበርበር ወንጀል ምርመራ ተከፈተባቸው
Sputnik አፍሪካ
የቀድሞው የሞሪሸስ ማዕከላዊ ባንክ ገዥ በማጭበርበር ወንጀል ምርመራ ተከፈተባቸው የሞሪሸስ ፖሊስ በአሁኑ ጊዜ ከሀገር ውጭ ናቸው የተባሉት የቀድሞ የማዕከላዊ ባንክ ገዥ ሃርቬሽ ኩማር ሴጎላም ላይ የእስር ማዘዣ አውጥቷል። የእስር ማዘዣው የገንዘብ... 15.12.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-12-15T17:43+0300
2024-12-15T17:43+0300
2024-12-15T18:14+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
የቀድሞው የሞሪሸስ ማዕከላዊ ባንክ ገዥ በማጭበርበር ወንጀል ምርመራ ተከፈተባቸው
17:43 15.12.2024 (የተሻሻለ: 18:14 15.12.2024)
ሰብስክራይብ