ከጎርጎሮሳውያኑ ታህሳስ 2025 ጀምሮ ቦሊቪያ እና ኩባ የብሪክስ አጋር ሀገራት እንደሚሆኑ ተገለፀ

ሰብስክራይብ
ከጎርጎሮሳውያኑ ታህሳስ 2025 ጀምሮ ቦሊቪያ እና ኩባ የብሪክስ አጋር ሀገራት እንደሚሆኑ ተገለፀ "ቦሊቪያ እና ኩባ ግብዣ ከቀረበላቸው ሀገራት መካከል ይገኙበታል። እርግጠኞች ነን የብሪክስ አጋር ሀገር በመሆናቸው ከብሪክስ ጋር የሚኖራቸው ሁሉም ነገር ይስራላቸዋል" በማለት የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ሰርጌ ረያብኮቭ ተናግረዋል። ረያብኮቭ አክሎም ግብዣ ከቀረበላቸው ሀገራት ጋር ያለው  የማስተባበር ሂደት አሁንም እየቀጠለ ሲሆን ነገርግን በድርጅቱ ውስጥ ያለው የሩሲያ የፕሬዝዳንትነት ጊዜ ሲያልቅ ሂደቱም ፍፃሜው የሚያግኝ ይሆናል በማለት ተናግረዋል። "እርግጥ ነው ወደ ኋላ ያለ የለም የሚኖርም አይኖርም። ለሁሉም ግብዣው ለቀረበላቸው ሀገራት ፤ ይሄ ትልቅ፣  ወሳኝ ተስፋ ያለው ነው ሰለሆነም ከዚህ በኋላ አስፈላጊውን ዝርዝር ለማውጣት በጣም ትንሽ ቀናቶች ቀርተውናል" በማለት ረያብኮቭ አክሏል።የብሪክስ አጋርነት ለሙሉ አባልነት  እንደ አማራጭ ያገለግላል ፤ ይህም አጋር ሀገራቱ ከመምረጥ መብት ውጭ ከብሪክስ አባላት ጋር ትብብር እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0