ባለፉት 5 ዓመታት የቡና ምርት መጠንን ከነበረበት 500 ሺህ ቶን በእጥፍ ማሳደግ ተችሏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ

ሰብስክራይብ
ባለፉት 5 ዓመታት የቡና ምርት መጠንን ከነበረበት 500 ሺህ ቶን በእጥፍ ማሳደግ ተችሏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹባለፉት 5 ዓመታት የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ በተከናወኑ ስራዎች ዓመታዊ የቡና ምርት መጠንን ከነበረበት 500 ሺህ ቶን በእጥፍ ማሳደግ ተችሏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።ጠ/ሚሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ፤ "ኢትዮጵያ የቡና መገኛ ብቻ ሳትሆን ከፍተኛ ቡና አምራች ሀገር ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል" ብለዋል።ከገቢ አንጻርም በተጠናቀቀው የ2016 በጀት ዓመት ከቡና ወጪ ንግድ ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ጠቅሰው፤ በተያዘው በጀት ዓመት ደግሞ ይህን አሃዝ ወደ 2 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ለማድረግ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን  ገለጸዋል።እቅዱን ለማሳካት የሚያስችሉ አበረታች ውጤቶች ከወዲሁ እየተመዘገቡ ነው ያሉት ዐቢይ  ዘመናዊ የቡና መስኖ ልማትና በማሽን የታገዘ የቡና ለቀማ በማካሄድ በሄክታር እስከ 60 ኩንታል ማግኘት መቻሉም  ለዚሁ ስኬት ጥሩ ማሳያ ነው ብለዋል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0