ኢኮዋስ ለቀጠናው መረጋጋት ሲባል ከሳህል ሀገራት ህብረት ጋር ሊተባበር ይገባል ስትል ሴኔጋል አሳሰበች

ሰብስክራይብ
ኢኮዋስ ለቀጠናው መረጋጋት ሲባል ከሳህል ሀገራት ህብረት ጋር ሊተባበር ይገባል ስትል ሴኔጋል አሳሰበች ከሳህል ሀገራት ጋር ቀጣይነት ያለው ትብብር አስፈላጊ እንደሆነ የገለጹት የሴኔጋል ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ፤ ትብብሩ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት፣ የስደት ጉዳዮችን ለመፍታት እና የንግድ ግንኙነቶችን ለማዳበር ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። የሳህል ሀገራት ህብረት የሽብር ስጋት እንደተደቀነበትና በአባላቱ መካከል ጠንካራ ግንኙነት እንዲኖር ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም ተናግረዋል። ቡርኪናፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር የውጭ ተጽእኖ እና ብሔራዊ ጥቅሞቻቸው ላይ ስጋት ደቅኗል በማለት ከኢኮዋስ መውጣታቸውን ተከትሎ፤ በኢኮዋስ እና በኤኢኤስ መካከል ያለው ግንኙነት እንደተበላሸ ይነገራል። የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ቦላ ቲኒቡ የሴኔጋሉ መሪ የኤኢኤስ ሀገራት ወደ ኢኮዋስ የሚመለሱበትን ሁኔታ እንዲያመቻቹ መጠየቃቸው የሚታወስ ነው።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0