የእስራኤል ጦር ከሶሪያ ጋር በሚያዋስነው ድንበር ላይ በሚገኘው የግጭት መከላከያ ዞን ወታደሮቹን እንዳሰማራ ገለጸ

ሰብስክራይብ
የእስራኤል ጦር ከሶሪያ ጋር በሚያዋስነው ድንበር ላይ በሚገኘው የግጭት መከላከያ ዞን ወታደሮቹን እንዳሰማራ ገለጸ "ታጣቂዎች በግጭት መከላከያ ዞን መግባታቸውን ጨምሮ በሶሪያ በቅርቡ የተከሰቱትን ሁኔታዎች ተከትሎ በተደረገው ግምገማ መሰረት የዜጎችን እና በጎላን ኮረብታ ላይ ያሉ ሰፈራዎችን ደህንነት ለመጠበቅ የእስራኤል መከላከያ ሃይል በግጭት መከላከያ ዞኑ እና በሌሎች በርካታ ቦታዎች ሰራዊቶቹን አሰማርቷል" ሲል አይዲኤፍ እሁድ እለት በሰጠው መግለጫ አስታውቋል። የመከላከያ ሃይሉ በሶሪያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ እንደማይገባም ተናግሯል። ህዳር 20 ቀን ሶሪያ መንግሥት ላይ መጠነ ሰፊ ዘመቻ የከፈቱት ታጣቂ ቡድኖች፤ ከኢድሊብ ተነስተው ወደ አሌፖ እና ሃማ ከተሞች ገስግሰዋል። ከአንድ ቀን በኋላ የሶሪያ ሁለተኛዋ ትልቅ ከተማ አሌፖ፤ ከ2011 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ በመሉ በታጣቂዎቹ ቁጥጥር ስር ገብታለች። ታጣቂዎቹ እሁድ ጠዋት ዋና ከተማዋ ደማስቆ መግባታቸው ተሰምቷል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0