የሶሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር በሀገሪቱ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ መጀመሩንና ከታጣቂዎች ጋር ግንኙነት መፍጠራቸውን ገለጹ

ሰብስክራይብ
የሶሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር በሀገሪቱ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ መጀመሩንና ከታጣቂዎች ጋር ግንኙነት መፍጠራቸውን ገለጹ በሶሪያ ስላለው ሁኔታ እስካሁን የታወቁ ነገሮች፦🟠 የሶሪያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞሐመድ ጋዚ ጃላሊ የሩሲያ ጦር በሀገሪቱ ውስጥ ያለውን ቆይታ በተመለከተ አዲሱ መንግሥት እንደሚወስን ገልጸዋል። 🟠 ባለስልጣኑ ፕሬዝዳንት አሳድ የት እንዳሉ እንደማያውቁ፣ ለመጨረሻ ጊዜ ያገኟቸው ቅዳሜ አመሻሽ ላይ እንደሆነ እና አሁን "በሶሪያ ታሪክ ውስጥ አዲስ ዘመን ጀምሯል" ብለዋል። 🟠 የሶሪያ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የት እንዳሉ እንደማያውቁ ተናግረዋል። 🟠 የሶሪያ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ታጣቂዎቹ በደማስቆ ለቀሩት የካቢኔ አባላት ደህንነት ዋስትና እንደሚሰጡ ቃል መግባታቸውን ይፋ አድርገዋል። 🟠 የእስራኤል ጦር ከሶሪያ ጋር በሚያገናኘው ድንበር የመከላከያ ቀጠና ውስጥ የታጣቂዎች ሰርጎ መግባት ስጋት በመኖሩ "የዜጎችን እና በጎላን ኮረብታ ላይ ያሉ ሰፈራዎችን ደህንነት ለመጠበቅ" ሰራዊቱን እንደሚያሰማራ አረጋግጧል። 🟠 የእስራኤል ጦር በሶሪያ እየተካሄደ ባለው ድርጊት ጣልቃ እንደማይገባ አጽንኦት ሰጥቷል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0