የዓለም ጤና ድርጅት በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ያልታወቀ ገዳይ በሽታን መመርመር እንደጀመረ አስታወቀ

ሰብስክራይብ
የዓለም ጤና ድርጅት በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ያልታወቀ ገዳይ በሽታን መመርመር እንደጀመረ አስታወቀ የዓለም ጤና ድርጅት በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ክዋንጎ ግዛት የተከሰተውን ገዳይ በሽታ ለመመርመር ባለሙያዎችን እንደላከ ገልጿል። የበሽታውን መንስኤ ለማወቅ የሚረዱ የህክምና ቁሳቁሶችን እና የምርመራ መሳሪያዎችን እንደሚያቀርቡ ተገልጿል። የዓለም ጤና ድርጅት በሽታውን ለመለየት የላብራቶሪ ምርመራ እያካሄደ ሲሆን ለተጎዱ ማህበረሰቦች ቅድሚያ በመስጠት ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ድርጅቱ ተጨማሪ መረጃ ሲገኝ ቀሪ መረጃዎችን እንደሚሰጥ ቃል ገብቷል። "የህመሙን መንስኤ ለማወቅ፣ የመተላለፊያ መንገዶችን ለመረዳት እና ተገቢውን ምላሽ በተቻለ ፍጥነት ለመስጠት ጥረት እየተደረገ ነው" ሲሉ የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር ማትሺዲሶ ሞኢቲ ተናግረዋል። እንደ የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ፤ በክዋንጎ ፓንዚ ጤና ዞን በተከሰተው በሽታ 394 ሰዎች ሲያዙ 30 ሰዎች ሞተዋል። የአካባቢው ባለስልጣናት 143 ሰዎች ማንነቱ ባልታወቀ በሽታ ህይወታቸውን እንዳጡ በህዳር ወር አስታውቀዋል። የበሽታው ምልክቶች ራስ ምታት፣ ሳል፣ ትኩሳት፣ የመተንፈስ ችግር እና የደም ማነስ ይገኙበታል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0