ኒጀር የሶሜር ዩራንየም ማበልፀጊያን በቁጥጥር ስር ማዋሏን የፈረንሳዩ ድርጅት ገለፀ

ሰብስክራይብ
ኒጀር የሶሜር ዩራንየም ማበልፀጊያን በቁጥጥር ስር ማዋሏን የፈረንሳዩ ድርጅት ገለፀየፈረንሳይ መንግሥት የኑክሌር ነዳጅ ድርጅት የሆነው ኦራኖ በሶሜር የዩራንየም ማበልፀጊያ ውስጥ 63 በመቶ ድርሻ ይዞ ነበር።በጎርጎሮሳዊያኑ ሰኔ 2024 የተፈፀመው ማዕድን ማውጫ ፍቃድ  መነጠቅ ፤ የውጭ ንግድ እንዲከለከል ቅስቀሳን ያደረገ ሲሆን ይህም ባለፈው ጥቅምት ወር በገንዘብ እና ሎጅስቲክ እጥረት ምክንያት ስራው እንዲቀዛቀዝ አድርጎታል። ኦራኖ በማበልፀጊያው ላይ ያለውን ቁጥጥር እንዳጣ አረጋግጧል። ይህ የተከሰተው ለወታደራዊ መንግስቱን እውቅና አልሰጥም ባለችው በፈረንሳይ እና ኒጀር መካከል ያለው ግንኙነት ውጥረት በሰፈነበት ወቅት ነው። የኒጀር መንግስት ካወጣቸው ቁልፍ ፖሊሲዎች አንዱ የውጭ ሀገራት የማዕድን አበልፃጊ ድርጅቶች ላይ ግምገማ በማድረግ በተጨማሪም  የደንቦች  ማሻሻያ በማድረግ ሀገሪቷ በዩራኒየም ማበልፀጊያዎች ላይ ያላትን ድርሻ ጉልህ በሚሆን መልኩ ማሳደግ ነው። ከአለም የዩራኒየም ምርት አራት በመቶ የሚሆነውን የምታቀርበዉ ኒጀር ናት።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0