የሶሪያ ፕሬዝዳንት ባሽር አል-አሳድ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት የአጋር ሀገራት ድጋፍ አስፈላጊ እንደሆነ ተናገሩ

ሰብስክራይብ
የሶሪያ ፕሬዝዳንት ባሽር አል-አሳድ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት የአጋር ሀገራት ድጋፍ አስፈላጊ እንደሆነ ተናገሩ"ፕሬዝዳንት አሳድ የሶሪያ ህዝብ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ሁሉንም ዓይነት ሽብርተኝነት መቋቋም እንደቻለ እና አሁን ከምንጊዜውም በላይ ሽብርተኝነትን ለማጥፋት ቆርጦ መነሳቱን አብራርተው፤ ከውጪ የሚደገፉ የሽብር ጥቃቶችን ለመከላከል የአጋር እና ወዳጆች ድጋፍ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል" ሲል የሶሪያ መሪ ጽህፈት ቤት መግለጫ ተነቧል።የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አባስ አራግቺ፤ ከሶሪያው ፕሬዝዳንት ጋር ባደረጉት ውይይት፤ ሶሪያ ከዚህ ቀደም እንዳደረገችው ሁሉ አሁንም አሸባሪ ቡድኖችን እንደምታሸንፍ ገልፀው፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያገረሸ የመጣው የሽብር ተግባር የመካከለኛውን ምስራቅ ጸጥታ ለማወክ እና ለማዳከም የሚደረግ የጠላቶች ሴራ አካል ነው ማለታቸውን የኢራን መንግሥት ገልጿል፡፡የኢራኑ ፋርስ የዜና ወኪል፤ የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ከሶሪያ ፕሬዝዳንት ባሻር አል-አሳድ ጋር በደማስቆ ተገናኝተው ስለ ሶሪያ ወቅታዊ ሁኔታ፤ በተለይም የጨመረውን የሽብርተኝነት እንቅስቃሴ በተመለከተ መወያየታቸውን እሁድ እለት ዘግቧል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0