በጊኒ የተካሄደ የእግር ኳስ ግጥሚያ ወደ ሐዘን ተለወጠ

ሰብስክራይብ
በጊኒ የተካሄደ የእግር ኳስ ግጥሚያ ወደ ሐዘን ተለወጠበንዘሬኮሬ እና በላቤ መካከል እሁድ እለት የተካሄደው የእግር ኳስ ግጥሚያ በተከሰተ ግጭት ምክንያት ወደ ሐዘን ተለውጧል፡፡ ሁለት ቀይ ካርዶች እና ለንዘሬኮሬ የተቆጠረ ጎልን ጨምሮ አወዛጋቢ የዳኝነት ውሳኔዎች ተቃውሞ አስነስተዋል፡፡ደጋፊዎች ድንጋይ መወርወር ሲጀምሩ ውጥረቱ እየተባባሰ በመምጣቱ የጸጥታ ሃይሎች በአስለቃሽ ጭስ ምላሽ ሰጥተዋል። በመጨረሻዎቹ ሰኮንዶች የፍፁም ቅጣት ምት ውሳኔ ከተላለፈ በኋላ ስታዲየሙ የተወረረ ሲሆን በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎች መሞታቸውን የአካባቢው ምንጮች ገልጸዋል። የሟቾች ቁጥር እየተመዘገበ መሆኑን የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አረጋግጠዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0