የቀድሞዋ ቀዳማዊት እመቤት ሲሞን ኢሂቬት ባግቦ በኮትዲቯር ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እጩ ተወዳዳሪ መሆናቸውን ገለጹ

ሰብስክራይብ
የቀድሞዋ ቀዳማዊት እመቤት ሲሞን ኢሂቬት ባግቦ በኮትዲቯር ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እጩ ተወዳዳሪ መሆናቸውን ገለጹ የቀድሞው የፕሬዝዳንት ሎረንት ባግቦ የቀድሞ ባለቤት፤ በፓርቲያቸው የብቁ ትውልድ ንቅናቄ ጉባኤ ላይ ለ2025 ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እጩ መሆናቸውን ይፋ አድርገዋል። "ጥቅምት 2025 በሚካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እጩ ለመሆን ተስማምቻለሁ፤ ምክንያቱም እያንዳንዱ ኮትዲቯራዊ በምንም ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ይሁን፤ ፍላጎቱ ካለው የትኛውንም ፈተና በመሻገር ለማለም፣ ለመፍጠር፣ ለመገንባት እና ስኬታማ ለመሆን እንደሚችል ከልብ አምናለሁ" ብለዋል። የቀድሞ ባለቤታቸው ሎረንት ባግቦ፤ በሀገሪቱ ፍርድ ቤቶች በተላለፈባቸው ፍርድ ምክንያት ብቁ ባይሆኑም፤ ፓርቲያቸው የአፍሪካ ሕዝቦች ፓርቲ እጩ አድርጎ መርጧቸዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0