ጋቦን የሕዝበ ውሳኔውን የመጨረሻ ውጤት በመቀበል አዲስ ሕገ-መንግሥት አፀደቀች "91.64% መራጭ የሕገ-መንግሥቱን ረቂቅ ሲደግፍ 8.36% ተቃውሞታል [...] የምርጫ ተሳታፊዎች ቁጥር 54.18% ነበር" ያሉት የጋቦን የሽግግር ሕገ-መንግሥታዊ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ዲዩዶኔ አባአ ኦዎኖ፤ ፍርድ ቤቱ ድምፁ እንዲሻር የሚጠይቅ አቤቱታ እንዳልደረሰው ጠቁመዋል። የተረጋገጠው የህዳር 7ቱ ህዝበ ውሳኔ ውጤት፤ ከሁለት ሳምንት በፊት በጋቦን የሀገር ውስጥ እና የደህንነት ሚኒስትር ኸርማን ኢሞንጋውልት ከታወጀው ቅድሚያ ውጤት በአንድ አስረኛ ነጥብ ይለያል። የሕገ-መንግሥታዊው ፍርድ ቤት ውሳኔ ይግባኝ ሊቀርብበት አይችልም። አዲሱ ሕገ-መንግሥት፤ የፕሬዝዳንቱን ሥልጣን የሚያጠናክር ሲሆን የመንግሥት ተቋማትን ሥልጣን ይቀንሳል። አንዴ ብቻ በድጋሚ የመመረጥ መብት የሚሰጥ የሰባት ዓመት የፕሬዝዳንታዊ የስልጣን ዘመን ይመሰርታል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ተሰርዞ ሥራው ለምክትል ፕሬዝዳንቱ ተሰጥቷል። ወታደራዊ አገልግሎት ግዴታ ሆኗል። የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ የተከለከለ ነው። ፈረንሳይኛ ቋንቋ ደግሞ የስራ ቋንቋ ይሆናል። የአዲሱ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 172፤ ሕጉ የሪፐብሊኩ ቀጣይ ፕሬዝዳንት ነሐሴ 2025 በሚካሄደው ምርጫ ከተመረጡ በኋላ፤ ጋቦን ውስጥ ተግባራዊ እንደሚሆን ይደነግጋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ጋቦን የሕዝበ ውሳኔውን የመጨረሻ ውጤት በመቀበል አዲስ ሕገ-መንግሥት አፀደቀች
ጋቦን የሕዝበ ውሳኔውን የመጨረሻ ውጤት በመቀበል አዲስ ሕገ-መንግሥት አፀደቀች
Sputnik አፍሪካ
ጋቦን የሕዝበ ውሳኔውን የመጨረሻ ውጤት በመቀበል አዲስ ሕገ-መንግሥት አፀደቀች "91.64% መራጭ የሕገ-መንግሥቱን ረቂቅ ሲደግፍ 8.36% ተቃውሞታል [...] የምርጫ ተሳታፊዎች ቁጥር 54.18% ነበር" ያሉት የጋቦን የሽግግር ሕገ-መንግሥታዊ ፍርድ... 30.11.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-11-30T11:56+0300
2024-11-30T11:56+0300
2024-11-30T12:04+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий