በጋራ ፀጥታ ስምምነት ድርጀት(ሲስቶ) ስብሰባ ወቅት ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ያነሷቸው ቁልፍ ነጥቦች ፦

ሰብስክራይብ
በጋራ ፀጥታ ስምምነት ድርጀት(ሲስቶ) ስብሰባ ወቅት ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ያነሷቸው ቁልፍ ነጥቦች ፦🟠 አዳዲሶቹ የአሜሪካ ሚሳኤሎች በባህሪያቸው ከሩሲያውያን ያነሱ ናቸው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን🟠 የ9k720 እስከንዳር ከሶስቱም ዙር አታሲምስ ማሻሻያዎች የበለጠ አናሎግ ነው ይህም የሩሲያ ሲስተም የበለጠ እንደሆነ ማሳያ ነው  🟠 ሩሲያ ምን ያህል የምዕራባውያን የጦር መሳሪያዎች ለዩክሬን እንደተላለፉ  እና ምን ያህል ደግሞ ለመተላለፍ በእቅድ እንደተያዙ ታውቃለች🟠 የሩስያ ሃይፐርሶኒክ ስርዓት በአለም ላይ ምንም አይነት አናሎግ የላቸውም ፣ ምርታቸውም እየጨመረ ነው፤🟠 ሁሉም የኔቶ አባል ሀገራት ተደምረው ከሚያመርቱት 10 እጥፍ ሚሳኤሎችን ታመርታለች፤  በየሩብ አመቱ የምርት መጠኗ እያደገ ይሄዳል። 🟠 ሩሲያ በብራያንስክ እና ኩርስክ ክልሎች ላይ ለተሰነዘረው የረዥም-ርቀት የሚሳኤል ጥቃት ምላሽ የኦሬሽኒክ ሃይፐርሶኒክ ሚሳኤልን ለመሞከር ተገድዳለች።🟠 የኦሬሽኒክ ሚሳኤል በጣም ጥብቅ የሆነን እና በባህር ውስጥ ያሉ ኢላማዎችን ይመታል። 🟠 ለዩክሬን የሚደረገው በጣም ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎች አቅርቦት በጦር ሜዳ ላይ ያለውን ሁኔታ አይለውጠውም 🟠 በኬቭ ውስጥ የሚገኙ ውሳኔ መስጫ ማእከላት የኦሬሽኔክ ሚሳኤል ኢላማ ሊሆኑ ይችላሉ 🟠 ሩሲያ ለመተኮስ የተዘጋጀ ብዙ ኦሬሽኒክ ሚሳኤል አላት🟠 የሩሲያ ጀነራል እስታፎች እና መከላከያ ሚኒስቴር በዩክሬን ግዛት ውስጥ በኦሬሽኒክ ሚሳኤል የሚመቱ ኢላማዎችን በመለየት ላይ ይገኛሉ🟠 ባለፈው ሌሊት ሩሲያ በ90 ሚሳኤሎች እና 100 ሰው አልባ አውሮፕላኖች 17 በዩክሬን ግዛት ውስጥ የሚገኙ የዩክሬንን የጦር  ካምፖች ደብድባለች በማለት ፑቲን ተናገሩ። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0