ኢትዮጵያ 3ተኛ የመሬት ምልከታ ሳተላይት ለማምጠቅ ከቻይናው ተቋም ጋር ስምምነት ተፈራረመች

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ 3ተኛ የመሬት ምልከታ ሳተላይት ለማምጠቅ ከቻይናው ተቋም ጋር ስምምነት ተፈራረመችየኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት እና ከቻይናው ሻንጋይ ኢንጂነሪንግ ሴንተር ጋር የኢትዮጵያን 3ኛ ሳተላይት ለማምጠቅ የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙስምምነቱ የተደረገው ETRSS-2 የሚል ስያሜ የተሰጣትን ሳተላይት በጋራ አልምቶ ለማምጠቅ ነው መሆኑን ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ዘግቧል።የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዲሳ ይልማ በስምምነቱ መሰረት የ18 ወራት የማልማት ስራ እንደሚከናወንና የመሬት ምልከታ ሳታላይት ለማምጠቅ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።ኢንስቲትዩቱ ዘንድሮ 12 ሜትር የመሬት ምልከታ ሳተላይት መረጃ መቀበያ ግራውንድ ስቴሽን ገንብቶ ወደ ስራ እየገባ መሆኑንም አከለው ተናግረዋል።በመስኩ ያለውን የተማረ የሰው ሀይል ችግር ለመቅረፍም ከአዲስ አበባ ዪኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር እስከ ሶስተኛ ዲግሪ ስልጠና እንዲሰጥ እየተደረገ መሆኑም ዘገባው አመላክቷል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ   @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0