የሩሲያው የኒኩለር ኃይል ድርጅት የኃይል መፍትሄዎችን ለአህጉሪቱ ለማቅረብ ከአፍሪካ ጋር ያለውን አጋርነት አድሷል የሮሳቶምስ ሀላፊ እንደተናገሩት

ሰብስክራይብ
የሩሲያው የኒኩለር ኃይል ድርጅት የኃይል መፍትሄዎችን ለአህጉሪቱ ለማቅረብ ከአፍሪካ ጋር ያለውን አጋርነት አድሷል የሮሳቶምስ ሀላፊ እንደተናገሩት " እንደማስበዉ በመሀል ተስተጓጉሎ የነበረው የ እኛ (ሮሳቶም የሩሲያ የኒኩለር ኃይል ድርጅት) አሁን ወደ አፍሪካ ተመልስናል። እንደ እኔ አስተሳሰብ አፍሪካ ከኃይል ጋር በተያያዘ የሚያጋጥሟትን ችግሮች  ከሩሲያ ጋር በቅርበት በመስራት መፍታት ትችላለች" በማለት የደቡብ እና መካከለኛው አፍሪካ የሮሳቶም ዋና ስራ አስኪያጅ ረያን ኮለይር ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። የድርጅቱ ሀላፊ አፍሪካ እና ሩሲያ በተባበሩት የሶቭየት ህብረት ጊዜ ወደነበራቸው ኒኩሌርን የተመለከ ጠንካራ ግንኙነት ለመመለስ አሁን እድሉን አግኝተዋል ብለዋል። "ታዳሽ ሀይልን በተመለከ የተወሰነ የብስባሽ ማቀጣጠያ ሊያስፈልገን .... እኔ እንደማስበዉ ኒኩሌር (ኃይል ) አፍሪካ የሚያስፈልጋትን ያህል ኃይል እንድታገኝ ኢንዱስትሪዎቿም ሆነ ኢኮኖሚዋ እንዲያድግ ወሳኝ ሚና ይጫወታል" በማለት ድርጅታቸውን አፍሪካ ላይ እየሰራ ያለውን አስረድተዋል።ለረጅም ጊዜ ባፈራው ታማኝነት ምክንያት የኒኩለር ሀይል ማመንጫን ለውጭ ንግድ በማቅረብ ድርጅታቸው ሮሳቶምስ በአለም አቀፍ ደረጃ እየመራ መሆኑን በአፅንኦት አስረድተዋል። የብሪክስ ትብብር የኒኩለር ኃይል አማራጮችን በመፍጠር  ለአፍሪካ ጭምር ማቅረብ ይችላል  ፤ የጥምረቱ ሀገሮች በስራ ላይ ያለ እና እየተገነባ ያለ የኑኩለር ኅይል ማመንጫ ያላቸው እና አለም ላይ ተፅእኖ መፍጠር የሚችል ድርሻ ያላቸው በመሆናቸው ይህንን የሀገራት ጥምረት በተለየ መልኩ የኒኩሌር ኃይል ማልማት ላይ ሊሰራ ይገባል በማለት ኮለይር ያክላሉ።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0