ዩናይትድ ኪንግደም ከጥቂት ሳምንታት በፊት ለመጀመሪያ ጊዜ በጠቅላይ ሚኒስትር ስታርመር ፍቃድ ስቶርም ሻዶው ሚሳኤሎችን ወደ ኬቭ መላኳን ዘገባዎች ገለጹ

ሰብስክራይብ
ዩናይትድ ኪንግደም ከጥቂት ሳምንታት በፊት ለመጀመሪያ ጊዜ በጠቅላይ ሚኒስትር ስታርመር ፍቃድ ስቶርም ሻዶው ሚሳኤሎችን ወደ ኬቭ መላኳን ዘገባዎች ገለጹጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ዩናይትድ ኪንግደም በደርዘን የሚቆጠሩ የመጀመሪያ ዙር ስቶርም ሻዶው ተወርዋሪ ሚሳኤሎች ለዩክሬን ቢሰጡም ለህዝብ በይፋ አልተገለፀም ፤ ሚሳኤሎቹ የተላኩት ኬቭ የረጅም-ርቀት ሚሳኤሎችን ከጨረሰች በኋላ እና አሜሪካ እና የናይትድ ኪንግደም ፤ ዩክሬን ሩሲያ ላይ የረጅም ርቀት ሚሳኤሎችን እንድትተኩስ ከመፍቀዳቸው ከበርካታ ሳምንታት በፊት መሆኑን ብሉምበርግ ምንጮችን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።ነገር ግን ሚሳኤሎቹ ትክክለኛ ብዛት እና ወደ ዩክሬን የገቡበት ቀን አልተገለጸም። የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቀደም ሲል እንዳስታወቁት ዩክሬን በኩርስክ እና ብራያንስክ ክልሎች ውስጥ በጎርጎሮሳውያኑ ህዳር 19 የአሜሪካን የረጅም-ርቀት አታስምስ ሚሳኤሎችን እና የብሪታንያን የረጅም ርቀት ስቶርም ሻዶው ሚሳኤሎችን በመጠቀም ጥቃት ሰንዝራለች።በአጸፋ ምላሹም ሩሲያ በጎርጎሮሳውያኑ ህዳር 21 በዩክሬን ወታደራዊ-ኢንዱስትሪያል ድርጅቶች ላይ ጥምር ጥቃት በመሰንዘር በድኔፕሮፔትሮቭስክ የሚገኘውን ግዙፉን የሚሳኤል ቴክኖሎጂ እና የጦር መሳሪያ አምራች የኢንዱስትሪን  መታለች። ዉጊያ እንዲመስል በተፈጠረ ሁኔታ ውስጥ ኦርሽኒክ የተባለው የሩሲያ አዲስ የመካከለኛ ርቀት ሚሳይል ሙከራ አድርጓል ፤ ሙከራው የተካሄደው ኒውክሌር ባልሆነ የሃይፐርሶኒክ መሳሪያ በተገጠመለት ባላስቲክ ሚሳይል አማካኝነት ነው።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0