🪖 ኬቭ ሊያሰማራ ከፈለገው የሰው ሀይል ማሳካት የቻለው ሁለት ሶስተኛውን ብቻ እንደሆነ ሪፖርቶች አመላከቱ

ሰብስክራይብ
🪖 ኬቭ ሊያሰማራ ከፈለገው የሰው ሀይል ማሳካት የቻለው ሁለት ሶስተኛውን ብቻ እንደሆነ ሪፖርቶች አመላከቱስሙ ያልተጠቀሰ የዩክሬን ባለስልጣን ለዌስቴርን ጋዜጣ እንደገለፀዉ በጎርጎሮሳውያኑ ፀደይ 2025 የሚኖረው የወታደሮች ምልመላ አደገኛ ይሆናል ብሏል ። ሪፖርቱ እንዳመላከተው ከወታደሮች አብዛኛዎቹ በጣም ያረጁ ወይም በወታደራዊ ኦፕሬሽኖች የመሳተፍ ምንም አይነት መነሳሳት የሌላቸው ናቸው።በስም ያልተጠቀሰው ባለስልጣን ጨምሮም የዩክሬን ስልታዊ ድክመት በግልፅ የጦሩን በግንባር ላይ ያለውን ሞራል ጎድቶታል። እንደሚታየው የተወሰኑት ወታደሮች ይህ ግጭት የሚቋጭበት ብቸኛ መንገድ ዩክሬን ከሩሲያ ጋር በመደራደር ነው ወደሚለው ሀሳብ ማድላት ጀምረዋል። “ቼቸን” በሚባል መጠሪያ የሚጠራው የብርጌዱ ዋና መስሪያ ቤት መኮንን ለጋዜጣው እንዳስረዳው 70 በመቶ የሚሆኑት ወታደሮች ቀድሞውኑ የግዛት ስምምነት ለማድረግ ዝግጁ ነበሩ።ባለፈዉ ማክሰኞ ዜሌንስኪ ከ25 አመት በታች ለሆኑ ዩክሬናውያን የሚሆን የጦር አገልግሎት ይፋ አድርጓል ፤ በተመሳሳይም ከደረጃ እድገት ጋር ሳይያያዝ በቀላሉ ግለሰቦችን እድገት የሚያገኙበት መንገድ ተመቻችቷል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0