አዲሱ የሞሪሸስ ጠቅላይ ሚኒስትር የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እንደሚመሩ ተናገሩ የቀድሞውን መንግሥት የኢኮኖሚ አያያዝ ኦዲት እንደሚያደርጉ ቃል የገቡት ተመራጩ የሞሪሸስ ጠቅላይ ሚኒስትር ናቪን ራምጎላም፤ የገንዘብ ሚኒስትርነቱን ቦታ ራሳቸው እንደሚይዙ ተናግረዋል። "ተሰናባቹ መንግሥት ያደረሰውን ጉዳት ለመመርመር ኢኮኖሚውን ኦዲት እያደረግን ነው" ሲሉ የካቢኔ ሹመታቸውን ይፋ ካደረጉ በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። የራምጎላም ጥምር መንግሥት ከ62 የብሔራዊ ምክር ቤት መቀመጫዎች 60 የሚሆነውን በማሸነፍ ወሳኝ ድል ተጎናጽፏል። የመንግሥትን ፋይናንስ ኦዲት ለማድረግ እና በቀደመው የስልጣን ዘመናቸው (1995-2000 እና 2005-2014) የጀመሩትን የኢኮኖሚ አማራጮችን የማስፋት ጥረት ለማስቀጠል እንዳቀዱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
አዲሱ የሞሪሸስ ጠቅላይ ሚኒስትር የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እንደሚመሩ ተናገሩ
አዲሱ የሞሪሸስ ጠቅላይ ሚኒስትር የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እንደሚመሩ ተናገሩ
Sputnik አፍሪካ
አዲሱ የሞሪሸስ ጠቅላይ ሚኒስትር የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እንደሚመሩ ተናገሩ የቀድሞውን መንግሥት የኢኮኖሚ አያያዝ ኦዲት እንደሚያደርጉ ቃል የገቡት ተመራጩ የሞሪሸስ ጠቅላይ ሚኒስትር ናቪን ራምጎላም፤ የገንዘብ ሚኒስትርነቱን ቦታ ራሳቸው እንደሚይዙ... 23.11.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-11-23T15:43+0300
2024-11-23T15:43+0300
2024-11-23T16:14+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий