ጁባ ውስጥ ሐሙስ የተሰማው የተኩስ ልውውጥ በፀጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት እንደተከሰተ የደቡብ ሱዳን ጦር አስታወቀ የደቡብ ሱዳን ጦር ቃል አቀባይ ሜጀር ጄኔራል ሉል ሩዋይ ኮአንግ፤ ሐሙስ አመሻሽ በጁባ ቶንግፒኒ የመኖሪያ አካባቢ በሚገኘው የቀድሞ የስለላ ሀላፊ ጀነራል ኩር መኖሪያ አቅራቢያ ከባድ የተኩስ ልውውጥ እንደነበር ለሱዳን ፖስት ተናግረዋል። የተኩስ ልውውጡ ከቀድሞው የብሔራዊ ደኅንነት አገልግሎት ኃላፊ መታሰር ጋር የተያያዘ ነው በማለት ምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን የሰሩትን ዘገባ የጦር ኃይሉ ቃል አቀባይ አስተባብለዋል። ጄኔራል አኮል ኩር እንዳልታሰሩ እና በተኩስ ልውውጡ ወቅት መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ እንደቆዩ ገልጸዋል። የጦር ኃይሉ ቃል አቀባይ አክለውም፤ አለመግባባቱ የተፈጠረበት ምክንያት አለመታወቁን ተናግረዋል። "ሁለት ወታደሮች በጥይት ተመተው ቆስለዋል። የመከላከያ ሰራዊቱ አዛዥ ጄኔራል ሳንቲኖ ዴንግ ወል በፍጥነት ወደ ስፍራው በመሄድ ግጭቱ እንዲቆም ትዕዛዝ ሰጥተው ሁኔታውን መቆጣጠር ችለዋል" ያሉት ቃል አቀባዩ፤ "በተፈጠረው ሁኔታ ዙርያ ነገ ምርመራ እንደሚጀመር" ጠቁመዋል። ሜጀር ጄኔራል ኮአንግ፤ ሁኔታው በቁጥጥር ስር መዋሉንም ለአካባቢው ነዋሪዎች አረጋግጠዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ጁባ ውስጥ ሐሙስ የተሰማው የተኩስ ልውውጥ በፀጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት እንደተከሰተ የደቡብ ሱዳን ጦር አስታወቀ
ጁባ ውስጥ ሐሙስ የተሰማው የተኩስ ልውውጥ በፀጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት እንደተከሰተ የደቡብ ሱዳን ጦር አስታወቀ
Sputnik አፍሪካ
ጁባ ውስጥ ሐሙስ የተሰማው የተኩስ ልውውጥ በፀጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት እንደተከሰተ የደቡብ ሱዳን ጦር አስታወቀ የደቡብ ሱዳን ጦር ቃል አቀባይ ሜጀር ጄኔራል ሉል ሩዋይ ኮአንግ፤ ሐሙስ አመሻሽ በጁባ ቶንግፒኒ የመኖሪያ አካባቢ በሚገኘው... 22.11.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-11-22T17:03+0300
2024-11-22T17:03+0300
2024-11-22T17:34+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
ጁባ ውስጥ ሐሙስ የተሰማው የተኩስ ልውውጥ በፀጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት እንደተከሰተ የደቡብ ሱዳን ጦር አስታወቀ
17:03 22.11.2024 (የተሻሻለ: 17:34 22.11.2024)
ሰብስክራይብ