ደቡብ አፍሪካ ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በኔታንያሁ፣ ጋላንት እና ዴፍ ላይ ያወጣውን የእስር ማዘዣ በደስታ እንደምትቀበል ገለጸች

ሰብስክራይብ
ደቡብ አፍሪካ ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በኔታንያሁ፣ ጋላንት እና ዴፍ ላይ ያወጣውን የእስር ማዘዣ በደስታ እንደምትቀበል ገለጸች "ፍልስጤም ውስጥ ለሚፈፀሙ የሰብዓዊና የጦር ወንጀሎች ፍትህ ለማምጣት ትልቅ እርምጃ ነው" ሲል የደቡብ አፍሪካ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ትብብር ዲፓርትመንት ባወጣው መግለጫው ተናግሯል። ደቡብ አፍሪካ ዓለም አቀፍ ህግን ለማክበር ቁርጠኛ እንደሆነች በመግለፅ፤ ሁሉም ሀገራት የሮም ስምምነት ግዴታቸውን እንዲወጡ ጠይቋል። "ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የህግ የበላይነትን እንዲያስጠብቅ እና ለሰብዓዊ መብት ጥሰት ተጠያቂነትን እንዲያረጋግጥ እንጠይቃለን"ሲል መግለጫው አሳስቧል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK  ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0