የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ከ2.7 ቢልዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ የባቡር መስመር ግንባታ አስጀመሩ ፕሬዝዳንት ሙሴቬኒ የመሠረት ድንጋይ የመጣል ሥነ-ሥርዓቱ ላይ መገኘታቸውን፤ የባቡር ሐዲዱ የፕሬስ አገልግሎት አስታውቋል። "ካጉታ ሙሴቬኒ የ272 ኪሎ ሜትር የማላባ-ካምፓላ ስታንዳርድ ጌጅ የባቡር መስመር ግንባታን በይፋ አስጀምረዋል። ግንባታው በ8 ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። የባቡር መስመሩ ሲጠናቀቅ ከሞምባሳ ወደ ካምፓላ የሚደረገውን የጉዞ ጊዜ አሁን ካለው 14 ቀን ወደ 1 ቀን ይቀንሳል" ሲል የፕሬስ አገልግሎቱ በኤክስ የትስስር ገጹ ገልጿል። ፕሮጀክቱ፤ ለኡጋንዳ የትራንስፖርት ስርዓት ትልቅ ምዕራፍ እንደሚሆን እና ክልላዊ ውህደትን እንደሚያጠናክር፤ ፕሬዝዳንቱ በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተናግረዋል። የሥራ እና የትራንስፖርት ሚኒስትር ኤድዋርድ ካቱምባ ዋማላ፤ የቱርኩ ኩባንያ ያፒ መርኬዚ በፕሮጀክቱ ትግበራ ላይ እንደሚሳተፍ ጠቁመዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ከ2.
የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ከ2.
Sputnik አፍሪካ
የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ከ2.7 ቢልዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ የባቡር መስመር ግንባታ አስጀመሩ ፕሬዝዳንት ሙሴቬኒ የመሠረት ድንጋይ የመጣል ሥነ-ሥርዓቱ ላይ መገኘታቸውን፤ የባቡር ሐዲዱ የፕሬስ አገልግሎት አስታውቋል። "ካጉታ ሙሴቬኒ የ272... 22.11.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-11-22T10:24+0300
2024-11-22T10:24+0300
2024-11-22T10:44+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий