የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ከ2.

ሰብስክራይብ
የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ከ2.7 ቢልዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ የባቡር መስመር ግንባታ አስጀመሩ ፕሬዝዳንት ሙሴቬኒ የመሠረት ድንጋይ የመጣል ሥነ-ሥርዓቱ ላይ መገኘታቸውን፤ የባቡር ሐዲዱ የፕሬስ አገልግሎት አስታውቋል። "ካጉታ ሙሴቬኒ የ272 ኪሎ ሜትር የማላባ-ካምፓላ ስታንዳርድ ጌጅ የባቡር መስመር ግንባታን በይፋ አስጀምረዋል። ግንባታው በ8 ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። የባቡር መስመሩ ሲጠናቀቅ ከሞምባሳ ወደ ካምፓላ የሚደረገውን የጉዞ ጊዜ አሁን ካለው 14 ቀን ወደ 1 ቀን ይቀንሳል" ሲል የፕሬስ አገልግሎቱ በኤክስ የትስስር ገጹ ገልጿል። ፕሮጀክቱ፤ ለኡጋንዳ የትራንስፖርት ስርዓት ትልቅ ምዕራፍ እንደሚሆን እና ክልላዊ ውህደትን እንደሚያጠናክር፤ ፕሬዝዳንቱ በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተናግረዋል። የሥራ እና የትራንስፖርት ሚኒስትር ኤድዋርድ ካቱምባ ዋማላ፤ የቱርኩ ኩባንያ ያፒ መርኬዚ በፕሮጀክቱ ትግበራ ላይ እንደሚሳተፍ ጠቁመዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK  ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0