ኢትዮጵያ 100 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል በኬንያ በኩል ወደ ታንዛኒያ ለመላክ ማቀዷን ዘገባዎች አመላከቱ

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ 100 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል በኬንያ በኩል ወደ ታንዛኒያ ለመላክ ማቀዷን ዘገባዎች አመላከቱ በደቡባዊ ኢትዮጵያ ሶዶ የመነጨው የኤሌክትሪክ ሃይል፤ በኬንያ ሱስዋ ከተማ በኩል፤ በሰሜን ታንዛኒያ አሩሻ ይደርሳል ሲል የኬንያ ኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጆን ማቲቮን ጠቅሶ የምዕራብ ዜና አውታር ዘግቧል። ዘገባው አክሎም፤ በኢትዮጵያ እና ታንዛኒያ እንዲሁም በተከታይ በኬንያ እና በታንዛኒያ መካከል በዚህ ዙርያ ስምምነቶች መፈረማቸውን አመላክቷል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፤ በ2016 የበጀት ዓመት የሀገሪቱ የኤነርጂ ወጪ ንግድ 140 ሚሊዮን ዶላር መድረሱንና፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ16 በመቶ እድገት ማሳየቱን አስታውቋል። የኢትዩጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አሸብር ባልቻ የዕድገቱ ምክንያት እየጨመረ የመጣው የኢነርጂ ፍላጎት፤ በተለይም የመረጃ ትንተና እንደሆነ ጠቅሰው፤ ለጠቅላላ የወጪ ንግድ ገቢ 27 ሚልዮን ዶላር አስተዋጽኦ ማድረጉን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የ2016 በጀት ዓመት ባሳለፍነው ዘመን ሰኔ 30 ተጠናቋል፡፡ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK  ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0