የህዳር 10 ረፋድ አበይት የዓለም ዜናዎች፡- አለም የምትዳደርበት ሂደት መሻሻል ይኖርበታል ፤ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲርል ራማፎሳ ሪዩዲጄኔሮ ጂ-20 ጉባኤ ጎንዩሽ ላይ የተናገሩት። የአፍሪካ ሀገራት እና ሌሎች አለምአቀፍ ማህበራት በጂ-20 ስብስብ ላይ ያላቸው ሚና ማደግ አለበት ፦ በጂ-20 መግለጫ ላይ እንደተፃፈው የሩሲያ መንግስት የሱዳንን ግጭት ለመፍታት በዩናይትድ ኪንግደም እና ሴራሊዩን አማካኝነት ለተመድ የቀረበዉን የመፍትሄ ሀሳብ አትደግፍም ፤ ምክንያቱ ደግሞ የለንደን መንግስት በሀገሪቷ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ እንድትገባ እድል ይሰጣል ያሉት በተመድ የሩሲያ ቋሚ ተወካይ ምክትል የሆኑት ዲሚትሪ ፖለይንስክ ናቸው። ዩክሬን የረጅም- ርቀት ሚሳኤሎችን በሩሲያ ግዛት ላይ እንድትጠቀም አሜሪካን ፍቃድ መስጠቷል ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት በተመድ የሩሲያ ቋሚ ተወካይ ቫሲልይ ንብንዘያ እንደተናገሩት ፤ ባይደን የሚያጡት ነገር አይኖርም ነገርግን ለንደን እና ፓሪስ አውሮፖን ብዙ መዘዝ ወዳለው ግጭት ጎትተው እያስገቧት ነው ብለዋል። ከሩሲያ መከላከያ ሚኒሰትር በተገኘ መረጃ መሰረት በዩክሬን እየተደረገ ባለው ልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽን ከተጀመረ ጀምሮ ከ900,000 በላይ ወታደሮች መገደላቸውን እና መቁሰላቸውን ያሳያል። የአሜሪካን መንግስት ለዩክሬን አዲስ ዙር የጦር መሳሪያ እርዳታ በቅርብ ቀን ሊያደርግ ነው ፤ በማለት በተመድ የአሜሪካን ቋሚ ተወካይ የተናገሩ ሲሆን የሚሰጠውን የእርዳታ ዝርዝር ከመናገር ተቆጥበዋል። የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሰርጌ ላቭሮቭ ከቻይና አቻቸው ዋንግ ዪ ጋር በቻይና እና በሩሲያ መሀከል የተደረገውን ስምምነት ተግባራዊ ስለማድረግ እና ስለቀጣይ የጋራ እንቅስቃሴዎች መወያየታቸውን የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒሰቴር አስታውቋል። የአሜሪካው ተመራጭ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስልጣናቸውን እንደያዙ ህገወጥ ስደተኞችን ለማስወጣት የጦር ሀይሉን እንደሚጠቀሙ እና በሀገሪቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንደሚያውጁ አረጋገጡ።ዜናውን በእንግሊዝኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ ለአንድሮይ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዩጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የህዳር 10 ረፋድ አበይት የዓለም ዜናዎች፡-
የህዳር 10 ረፋድ አበይት የዓለም ዜናዎች፡-
Sputnik አፍሪካ
የህዳር 10 ረፋድ አበይት የዓለም ዜናዎች፡- አለም የምትዳደርበት ሂደት መሻሻል ይኖርበታል ፤ የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲርል ራማፎሳ ሪዩዲጄኔሮ ጂ-20 ጉባኤ ጎንዩሽ ላይ የተናገሩት። የአፍሪካ ሀገራት እና ሌሎች አለምአቀፍ ማህበራት በጂ-20... 19.11.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-11-19T12:45+0300
2024-11-19T12:45+0300
2024-11-19T13:24+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий