የሱዳን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካን ኢኮኖሚ በማጠናከር እንዲሁም የተመጣጠነ የዓለም ኢኮኖሚ እንዲኖር ብሪክስ ሚና እንዳለው በአጽንዕኦት ገልጸዋል

ሰብስክራይብ
የሱዳን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካን ኢኮኖሚ በማጠናከር እንዲሁም የተመጣጠነ የዓለም ኢኮኖሚ እንዲኖር ብሪክስ ሚና እንዳለው በአጽንዕኦት ገልጸዋል "ብሪክስ መድረክ ነው፤ በጣም አስፈላጊ የሆኑ ሀገራት ስብስብ መድረክ ነው እናም በዓለም ላይ ኢኮኖሚያዊ እና ስትራቴጂካዊ መመጣጠን ለመፍጠር ፤  የተወሰኑ  ሀገራትን የበላይነት ለማስቀረት ... በተለይም የምዕራብያውያን ሀገራት ህብረት ለማስቀረት እጅግ አስፈላጊ ነው” ሲሉ የሱዳን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሁሴን አላሚን አልፋዲል አል ሃጅ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገለጹ።ሚንስትሩ በሶቺ በተካሄደው የ #ሩሲያአፍሪካ የሚኒስትሮች ኮንፍረንስ ጎን ለጎን፤ ብሪክስ የአፍሪካ አገራት ወደ አዲስ የኢኮኖሚ እድገት ደረጃ እንዲሸጋገሩ በማገዝ ጉልህ ሚና መጫወቱን ገልጸዋል። "ብሪክስ የአፍሪካ አገራት እንዲያድጉ ትልቅ ሚናም ይጫወታል" ያሉት ሚንስትሩ፤ የብሪክስን እንቅስቃሴ እና ተጽዕኖ ለማጠናከር  የአፍሪካ አገራት እና ሩሲያ የሚያደርጉትን የቅንጅት ጥረት እጽንዕኦት ሰጥተዋል። በተጨማሪም አል ሃጅ፤ ሩሲያ እና ቻይና በብሪክስ ማዕቀፍ ውስጥ አፍሪካን ከፍ ለማድረግ እና የብዝሃ_አለም ስርዓትን ለማጎልበት ያበረከቱትን ከፍተኛ አስተዋጽኦ አውቅ በመስጠት አድንቀዋል። በርካታ የአፍሪካ አገራት ብሪክስን ለማጠናከር ከሩሲያ ጋር በትብብር እየሰሩ በመሆኑ ይህ አጋርነት የኢኮኖሚ እድገትን እና ለአለም አቀፍ የኃይል መመጣጥን  የአፍሪካን ሚና መደገፍ እንደሚቀጥል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።ዜናውን በእንግሊዝኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ ለ አንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0