ሩሲያ በአፍሪካ የጂኦሎጂ ፍለጋዎችን ለማስፋፋት ዝግጁ መሆኗን ገለፀች

ሰብስክራይብ
ሩሲያ በአፍሪካ የጂኦሎጂ ፍለጋዎችን ለማስፋፋት ዝግጁ መሆኗን ገለፀችየሩሲያ ድርጅቶች በአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት የተለያዩ የጂኦሎጂ ፍለጋዎች ላይ ተሰማርተዋል። የሩሲያ መንግሰት የጂኦሎጂ ድርጅት ሮስጂኦሎጂያ የማእድን ትንበያውን እና ፍለጋውን  በቤኒን፣ ሱዳን፣ ጅቡቲ፣ አንጎላ እና የማእከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ውስጥ እያካሄደ መሆኑን የሩሲያው የተፈጥሮ ሀብቶች ሚኒስቴር አሌክሳንደር ኮዝሎቭ በ #ሩሲያአፍሪካ አጋርነት ፎረም የመጀመሪያው የሚኒስትሮች ኮንፈረስ ላይ ተናግረዋል። "ከስድስት በላይ እየለሙ ያሉ አዳዲስ ፕሮጀክቶች አሉ። እነርሱም በዙምባብዌ፣ በአልጄሪያ፣ በቻድ፣ በሞዛምቢክ፣ በሴራሊዮን እና በማሊ ናቸው። በቂ የሆነ ጥንካሬ እና ብቃት ስላለን በአህጉሪቷ ውስጥ ስራችንን ለማስፋፋት ዝግጁ ነን" በማለት ጨምሮ ተናግሯል። ኮዝሎቭ አክለውም ሌላ የሩሲያ ድርጅት በአፍሪካ ስራዎችን ለመስራት ፍላጎት አሳይቷል። " ከማእድን ፍለጋው በተጨማሪ ማእድናትን ለማቀናጀት እንዲሁም ውሰጣቸው ያለውን ለማወቅ የሚያግዙ ምርመራዎችን ያግዛሉ።" ካዝሎቭ አፅንኦት የሰጡበት ሌላው ጉዳይ የአፍሪካ ሀገራት ከሌሎች ጋር አብረው በመሆን የጥሬ እቃን በህብረት የአለም ገበያ በሚፈቅደው መሰረት የማቅረብ ጉዳይ ነው።ዜናውን በእንግሊዝኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ ለ አንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0