'በቴክኖሎጂ ያልታገዘ ግብርና መኖር የለበትም' ጊኒያዊዉ የቴክኖሎጂ ተማሪ 

ሰብስክራይብ
'በቴክኖሎጂ ያልታገዘ ግብርና መኖር የለበትም' ጊኒያዊዉ የቴክኖሎጂ ተማሪ  "የምንጠቀምባቸው ዘዴዎች ተመሳሳይ አይደሉም ። ሩሲያ ውስጥ ሁሉም ነገር በቴክኖሎጂ ነው ሚሰራው። አሁንም ድረስ አፍሪካ ውሰጥ በእጅ እና በጉልበት ነው እየተሰራ ያለው።" ይህንን ለስፑትኒክ አፍሪካ የተናገረው ሀገሩ ጊኒን በቴክኖሎጂ ለማገዝ  በሩሲያ እየተማረ ያለው ፋሲሌ ኮንዴ ነው።የሴንት ፒተርሰበረግ ዩንቨርሲቲ ካሊልግራንድ ቅርንጫፍ  አግሮኖሚ እያጠና ያለው ኮንዴ ዩንቨርሲቲውን የመረጠው በሚሰጠው ጥራት ያለው ስልጠና ምክንያት ነው ብሏል። ሀገሩን በቴክኖሎጂ ከማገዝ በተጨማሪ ወጣት ተመራቂዎች ወደ ግብርና  እንዲገቡ እየረዳቸው ነው።የሩሲያ ህዝብም ሆነ ዩንቨርሲቲዉ እንግዳ ተቀባይ ናቸው። በዩንቨርሲቲው የሚሰጠው ትምህርት ጥራት ያለው በመሆኑ ከዩንቨርስቲው ተመርቀዉ የወጡ ወጣቶች በጥሩ ደሞዝ ተቀጥረዋል። "ዩንቨርሲቲው ተማሪዎች ተግባራዊ ምርምር እንዲያደረጉ ያበረታታል።" ያለው ኮንዴ የመምህራኑ ተማሪዎች ሀሳባቸውን በነፃ እንዲገልጹ ማበረታታት አስተሳሰባቸውን እንዳስፋፋው ተናግሯል።ከትምህርት በተጨማሪ ኑሮ በሩስያ ተመጣጣኝ እና መኖሪያ ቤትም በጥሩ ሁኔታ እንደሚገኝ ተናግሯል። "ሩሲያ ለተማሪዎች ምቹ የሆነ የኑሮ ሁኔታ አላት" በማለት ያጠቃልላል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ ለ አንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0