ኢትዮጵያ ከ156 ዓመታት በፊት በዩናይትድ ኪንግድም የተወሰደ ታሪካዊ ቅርስ ማስመለሷ ተዘገበ"ከ156 ዓመታት በኋላ የኢትዮጵያ ታሪክ ቅርስ በመጨረሻም ወደ አገር ቤት ተመልሷል። በ1868 በመቅደላ ጦርነት ወቅት የተወሰደው የአጼ ቴዎድሮስ ሁለተኛ ጋሻ ወደ ኢትዮጵያ መመለሱን" የኢትዮጵያ ብሮድካስቲን ኮርፖሬት ዘግቧል። የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ጋሻውን ለማስመለስ ከአንድ ዓመት በላይ ጥረት ሲያደርግ እንደነበር ተገልጿል። ጋሻው በ2016 ዓ.ም. ለጨረታ ቀርቦ የነበረ ቢሆንም በባለስልጣኑ ጥረት እና የቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ የልጅ ልጅ ልዑል ኤርሚያስ ሳህለ-ሥላሴ ባደረጉት ድጋፍ ጨረታው እንዲሰረዝ ተደርጓል።ዘገባው እንዳመላከተው፤ መጭው ትውልድ ይህን የኢትዮጵያን ታሪክ ምዕራፍ እንዲማር ጋሻው አሁን በዘላቂነት ለእይታ ይቀርባል።“ጋሻው የአገሪቱን ቅርስ ወሳኝ ክፍል የሚያመላክት እና የአፄ ቴዎድሮስን አሻራ ማሳያ በመሆኑ የቅርሱ መመለስ ለኢትዮጵያ ታሪክ ዋሳኝ ክስተት መሆኑን እንደሚያመላክት” ኢቢሲ በአጽንዖት ገልጿል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ ለ አንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ኢትዮጵያ ከ156 ዓመታት በፊት በዩናይትድ ኪንግድም የተወሰደ ታሪካዊ ቅርስ ማስመለሷ ተዘገበ
ኢትዮጵያ ከ156 ዓመታት በፊት በዩናይትድ ኪንግድም የተወሰደ ታሪካዊ ቅርስ ማስመለሷ ተዘገበ
Sputnik አፍሪካ
ኢትዮጵያ ከ156 ዓመታት በፊት በዩናይትድ ኪንግድም የተወሰደ ታሪካዊ ቅርስ ማስመለሷ ተዘገበ"ከ156 ዓመታት በኋላ የኢትዮጵያ ታሪክ ቅርስ በመጨረሻም ወደ አገር ቤት ተመልሷል። በ1868 በመቅደላ ጦርነት ወቅት የተወሰደው የአጼ ቴዎድሮስ ሁለተኛ ጋሻ... 02.11.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-11-02T21:16+0300
2024-11-02T21:16+0300
2024-11-02T21:44+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
ኢትዮጵያ ከ156 ዓመታት በፊት በዩናይትድ ኪንግድም የተወሰደ ታሪካዊ ቅርስ ማስመለሷ ተዘገበ
21:16 02.11.2024 (የተሻሻለ: 21:44 02.11.2024)
ሰብስክራይብ