ማርክ ሩት አዲሱ የኔቶ ዋና ፀሀፊ ሆነው በይፋ ተሾመዋል

ሰብስክራይብ
ማርክ ሩት አዲሱ የኔቶ ዋና ፀሀፊ ሆነው በይፋ ተሾመዋል"ውድ ማርክ እባክህ ይህን ልዩ ጋቭል ተቀበል፤ የሰሜን አትላንቲክ ካውንስል ሊቀመንበር በመሆንህ ኃላፊነትህን ተረከብ " ሲሉ የኔቶ የቀድሞ ዋና ጸሃፊ ጄንስ ስቶልተንበርግ ለአዲሱ መሪ ስልጣን ባስረከቡበት ወቅት ተናግሯል። ዩክሬን በኔቶ ቦታ ማግኘት አለባት ሲሉ አዲሱ የኔቶ ዋና ፀሃፊ ማክሰኞ ዕለት በብራሰልስ በሚገኘው የኔቶ ዋና መስሪያ ቤት በተካሄደው የርክክብ ስነስርዓት ላይ ተናግረዋል። የሩት ሹመት የህብረቱን ፖሊሲ አይጎዳውም ፣ በተመሳሳይ መልኩ መስራቱን ይቀጥላል ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ በሹመቱ ዙሪያ የሩሲያን አቋም ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።"እኛ የምንጠብቀው የሰሜን አትላንቲክ አሊያንስ በተለመደው መንገድ መስራቱን እንደሚቀጥል ነው" ብለዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለ iOS በአፕ ስቶር ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0