የመስከረም 8 ረፋድ አበይት የዓለም ጉዳዮች፦

ሰብስክራይብ
የመስከረም 8 ረፋድ አበይት የዓለም ጉዳዮች፦ 🟠 የአየር መከላከያዎች 54 የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን እንዳወደሙ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ። 🟠 በሩሲያ ቤልጎሮድ ክልል ሼቤኪኖ ከተማ የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላን በአገልግሎት አውቶብስ ላይ ባደረሰው ጥቃት አራት ንፁሀን እንደቆሰሉ የክልሉ አስተዳዳሪ ተናገሩ። 🟠 በሊባኖስ በፔጃሮች የተካሄደው ኦፕሬሽን በእስራኤል የተቀነባበረ እንደሆነ መገናኛ ብዙሃን የአሜሪካ ባለስልጣናትን ጠቅሰው ዘገቡ። 🟠 ሰሜን ኮሪያ የባላስቲክ ሚሳኤል ሳታስወንጨፍ እንደማትቀር የጃፓን የባህር ጠረፍ ጥበቃን ጠቅሰው መገናኛ ብዙሃን አስነበቡ። 🟠 በሩሲያ ታታርስታን ሪፐብሊክ የዓለም አቀፍ አሸባሪ ድርጅት የሴቶች ህዋስ መጋለጡን የሩሲያ የፌደራል ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ። 🟠 የሰው ልጅ የኮከቦች በረራን የማይመራ ከሆነ የመጥፋት እጣ ፈንታ እንደሚጠብቀው የስፔስኤክስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኤለን መስክ ተናገረ።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለ iOS በአፕ ስቶር ለአንድሮይድ ስልኮች በGoogle Play ወይም በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0