የመስከረም 2 ምሽት አበይት የዓለም ሁነቶች፦

ሰብስክራይብ
የመስከረም 2 ምሽት አበይት የዓለም ሁነቶች፦ 🟠 የሩሲያ ፕሬዝዳንት የኢራን ከፍተኛ ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ፀሀፊ አሊ አክባር አህመዲያን ጋር ተገናኝተው ተወያዩ። 🟠 በሩሲያ የኩርስክ ግዛት በዩክሬን ጦር በተወረሩ አንዳንድ አካባቢዎች ማጎሪያ የሚመስሉ ካምፖች መሰራታቸውን የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመለከተ። 🟠 ዋርሶ ዩክሬን በሩሲያ ግዛት ላይ የረዥም ርቀት የሚሳኤል ጥቃት እንዳትፈጽም የተቀመጠው እገዳ እንዲነሳ ድጋፍ መስጠቷን የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከአሜሪካ አቻቸው ጋር ካካሄዱት ግኑኝነት በኋላ ተናገሩ። 🟠 ፖላንድ ኤፍኤ-50 የስልጠና እና የውጊያ አውሮፕላኖችን ከደቡብ ኮሪያ ብትገዛም ለውጊያ እንደማይሆን ታውቋል ሲሉ ምክትል የመከላከያ ሚኒስትር ሴዛሪ ቶምቺክ ገለጹ። 🟠 የብሪታኒያ የሀገር ውስጥ ጉዳዮች ጸሀፊ ዲያና ጆንሰን በሀገሪቱ የተንሰራፋውን የስርቆት ወረርሽኝ እና ፀረ-ማህበረሰብ ባህሪን አስመልክቶ ንግግር ባደረጉበት የፖሊስ መኮንኖች ኮንፈረንስ ላይ የኪስ ቦርሳቸው መሰረቋን መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ። 🟠 የስፔስኤክስ ድራጎን የጠፈር መንኮራኩር ቡድን አባላት ባለሙያ ባልሆኑ ሰዎች የመጀመሪያውን የጠፈር ጉዞ አደረጉ።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለ iOS በአፕ ስቶር ለአንድሮይድ ስልኮች በGoogle Play ወይም በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0