የሩሲያ ጦር ኃይል በዶንባስ ተጨማሪ አራት መንደሮችን መቆጣጠሩን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስቴር ገለጸ

ሰብስክራይብ
የሩሲያ ጦር ኃይል በዶንባስ ተጨማሪ አራት መንደሮችን መቆጣጠሩን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስቴር ገለጸ ነፃ የወጡት ጋሊትሲኖቭካ፣ ጊጎሮቭካ፣ ክራስኖጎሮቭካ እና ቮድያኖዬ በዶኔትዬትስክ ህዝቦች ሪፐብሊክ ውስጥ ይገኛሉ። ልዩ ወታደራዊ ዘመቻውን አስመልክቶ ሚኒስቴሩ በዕለታዊ ሪፖርቱ ያነሳቸው ተጨማሪ መግለጫዎች፡- 🟠 የሩሲያ አየር መከላከያ በ24 ሰዓት ውስጥ 175 የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ ጥሏል። 🟠 የሩሲያ ኃይል አሜሪካ ሰሩን ኤም270 ኤምኤልአርኤስ ባለብዙ አስወንጫፊ የሮኬት ስርዓት እና የድሮን ማምረቻ ፋብሪካን አውድሟል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0