የክሬምሊን ቃል አቀባይ በአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን ላይ ገደብ እንደሚጥል አስታወቀ

ሰብስክራይብ
የክሬምሊን ቃል አቀባይ በአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን ላይ ገደብ እንደሚጥል አስታወቀ " አፀፋዊ እርምጃዎች ሊኖሩ አይችሉም። በአሜሪካ ውስጥ የመንግስት የዜና ወኪል የለም፤ የመንግስት የቴሌቪዥን ጣቢያም የለም። መገናኛ ብዙሃኖቻቸው በሩሲያ ምድር ያላቸው ስርጭትን የሚገድቡ እርምጃዎችን ግን እንወስዳለን " ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።አንዳንድ ገደቦች ቀደም ብለው በሥራ ላይ መዋላቸውንም ጨምረው ገልጸዋል።የአሜሪካ የግምጃ ቤት ዲፓርትመንት ረቡዕ እለት በሮሲያ ስጎድኒያ የሚዲያ ቡድን፣ ሪያ ኖቮስቲ፣ አር ቲ፣ ስፑትኒክ እና ረኘትሌይ ላይ ማዕቀብ ጥሏል። ቅጣቱ የሮሲያ ሴጎድኒያ እና አር ቲ ዋና አዘጋጅ ማርጋሪታ ሲሞንያን እና ሌሎች በርካታ ከፍተኛ አመራሮች ስራቸውን እንዳያከናውኑ ያወከ ነው።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0