ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያሉ አለመግባባቶች በሰላማዊ መንገድ መፍትሄ እንዲያገኙ እና አንድነትን እንደምትደግፍ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አስታወቁ

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያሉ አለመግባባቶች በሰላማዊ መንገድ መፍትሄ እንዲያገኙ እና አንድነትን እንደምትደግፍ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አስታወቁሚኒስትሩ አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ ጠንካራ ማህበረሰባዊ ትስስር ያላቸው የክልሉ ህዝቦች ካለፉት ግጭቶች እና ጥላቻዎች ወጥተው በጋራ እድገት ዙሪያ ያሉ እድሎች ላይ መሥራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል። ታዬ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ድርድር መሻሻልን እንዳለ ጠቅሰው፤ ነገር ግን ግጭት ቀስቃሽ አስተያየቶች እና ድርጊቶች ጥረቶችን እንዳያበላሹ አስጠንቅቀዋል። ከጠላት ሃይሎች ጋር የሚደረገው ትብብር አጭር እይታ እና ውጤት የሌለው ነው ሲሉ ተችተው ኢትዮጵያ አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል። በሱዳንና በደቡብ ሱዳን ለሚደረገው የሰላም ጥረትን ኢትዮጵያ እንደምትደግፍ ገልፀው በእነዚህ ሀገራት መካከል ዘላቂ ሰላም መምጣት እንዳለበት አሳስበዋል። ከዚ ውጪ፣ ሚኒስትሩ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነትን ለማፅደቅ ኢትዮጵያ ያላትን “ጠንካራ” ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0