ዩክሬን በሩሲያዋ ቤልጎሮድ ከተማ በፈፀመቸው ጥቃት የቆሰሉ ንፁሀን ዜጎች ቁጥር 46 መድረሱን ገዥው ተናገሩ

ሰብስክራይብ
ዩክሬን በሩሲያዋ ቤልጎሮድ ከተማ በፈፀመቸው ጥቃት የቆሰሉ ንፁሀን ዜጎች ቁጥር 46 መድረሱን ገዥው ተናገሩገዥው ቪያቼስላቭ ግላድኮቭ አርብ አመሻሽ ላይ እንዳሉት የአየር መከላከያዎች በቤልጎሮድ ክልል እና በአካባቢው ላይ በመከላከል ላይ ነበሩ፤ በዚህም በርካታ የአየር ኢላማዎች መትተው ጥለዋል። ጥቃቱ የተፈፀመው በቫምፓየር ባለብዙ ማስወንጨፊያ ሮኬት ስርዓቶች አማካኝነት መሆኑን እና በጥቃቱ አምስት ሰዎች መሞታቸውን እንዲሁም 37 ደግሞ መቁሰላቸውን በኋላ ላይ ገዢው ተናግዋል። "በቤልጎሮድ ከተማ በዩክሬን ታጣቂ ሃይሎች በደረሰው ጥቃት እንደገና ንፁሀን ዜጎችን አጥተናል። 5 ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል ... 46 ሰላማዊ ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል ። በአሁኑ ጊዜ 37 ሰዎች በሆስፒታል ውስጥ ይገኛሉ ፣ ከእነዚህ ውስጥ ሰባቱ ህጻናት ናቸው። አንድ ልጅ በከባድ ሁኔታ ላይ ነው ያለው ”ሲሉ ግላድኮቭ በቴሌግራም ላይ በላኩት የቪዲዮ መልእክት ተናግሯል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0