የቡርኪናፋሶ ፕሬዝዳንት ለብሄራዊ ደህንነት ቅድሚያ በመስጠት ወደ ቻይና የሚያደርጉትን ጉዞ ሰረዙ

ሰብስክራይብ
የቡርኪናፋሶ ፕሬዝዳንት ለብሄራዊ ደህንነት ቅድሚያ በመስጠት ወደ ቻይና የሚያደርጉትን ጉዞ ሰረዙኢብራሂም ትራኦሬ በቅርቡ በባርሳሎሆ ላይ የተፈፀመውን ጥቃት ተከትሎ የብሄራዊ ደህንነት ችግሮችን ለመፍታት እንዲህ አይነት ውሳኔ ማሳለፍቸው ተዘግቧል። እ.አ.አ ከመስከረም 4-6 በቤጂንግ ሊካሄድ በታቀደው የቻይና አፍሪካ የትብብር ፎረም ላይ አይሳተፉም።እንደ ዘገባው ከሆነ በቡርኪናፋሶ ማዕከላዊ-ሰሜን ክልል ባርሳሎጎ ከተማ ላይ እ.አ.አ በነሀሴ 24 በደረሰው ጥቃት እስከ 200 የሚደርሱ ንፁሃን ዜጎች እና የጸጥታ አባላት ተገድለዋል። ይህ ክስተት በቡርኪናፋሶ እየተካሄደ ያለው ግጭት አንዱ አካል ሲሆን ከአልቃይዳ* እና ዳኢሽ* ጋር ግንኙነት ያላቸው ታጣቂ ቡድኖች ገጠራማ አካባቢዎች ዒላማ. በማድረግ ለከፍተኛ ብጥብጥ እና መፈናቀል ምክንያት ሆነዋል።* የአሸባሪ ድርጅቶች በሩሲያ እና በሌሎች በርካታ ሀገራት እገዳ ተጥሎባቸዋል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0