በናይጄሪያ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ባለፉት ሳምንታት 170 ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ዘገባዎች አመለከቱበሰሜናዊ ናይጄሪያ በሚገኙ አስር ግዛቶች በተከታታይ ቀናት በጣለ ዝናብ ሳቢያ በደረሰ የጎርፍ አደጋ በእርሻ መሬቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱንና የሀገሪቱን የምግብ እጥረት እንዳያባብስ ስጋት መፈጠሩን የምዕራቡ ዓለም ጋዜጣ ሰኞ እለት ዘግቧል። በተፈጥሮ አደጋው ከ200,000 በላይ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው እንደተፈናቀሉ የገለጸው ዘገባው ሰሜን ናይጄሪያ በጎርፉ በክፉኛው እንደተጎዳች አክሏል። ጋዜጣው የናይጄሪያ ብሔራዊ የአደጋ ጊዜ አስተዳደር ባለስልጣን ቃል አቀባይ ማንዞ ኢዝኪዬል "በሚቀጥሉት ቀናት ማእከላዊ ክፍሎች እንዲሁም ወደታች ወረድ ብሎ ደቡባዊ ክፍሎችም ተመሳሳይ ጎርፍ ይገጥማቸዋል" ማለታቸውን ጠቅሶ አስነብቧል። በናይጄሪያ በቅርቡ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ 2,000 ሰዎች እንደተጎዱ እና ከ100,000 ሄክታር በላይ የእርሻ መሬት መውደሙን ዘገባው አክሎ ገልጿል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
በናይጄሪያ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ባለፉት ሳምንታት 170 ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ዘገባዎች አመለከቱ
በናይጄሪያ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ባለፉት ሳምንታት 170 ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ዘገባዎች አመለከቱ
Sputnik አፍሪካ
በናይጄሪያ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ባለፉት ሳምንታት 170 ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ዘገባዎች አመለከቱበሰሜናዊ ናይጄሪያ በሚገኙ አስር ግዛቶች በተከታታይ ቀናት በጣለ ዝናብ ሳቢያ በደረሰ የጎርፍ አደጋ በእርሻ መሬቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱንና... 28.08.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-08-28T19:41+0300
2024-08-28T19:41+0300
2024-08-28T20:23+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
በናይጄሪያ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ባለፉት ሳምንታት 170 ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ዘገባዎች አመለከቱ
19:41 28.08.2024 (የተሻሻለ: 20:23 28.08.2024)
ሰብስክራይብ