ኬንያ የተባበሩት መንግሥታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮን ለመደገፍ ወታደሮቿን ወደ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ አሰማራች የኬንያ ፈጣን ምላሽ ኃይል (KENQRF 4) አራተኛው ክፍለ ጦር የመጀመርያው ቡድን ወደ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ አቅንቷል። ወታደሮቹ ታጣቂ ቡድኖችን በመዋጋት፣ ሲቪሎችን በመጠበቅ፣ ሰብዓዊ እርዳታዎችን በመደገፍ እና የቀድሞ ታጋዮችን ትጥቅ ማስፈታት እና መልሶ ማቋቋምን ጨምሮ በተለያዩ ስራዎች ላይ እንደሚሰማሩ የኬንያ መከላከያ ኃይል በመግለጫው አስታውቋል። ኃይሉ በታጣቂ ቡድኖች የሚታመሱትን ምስራቃዊ ግዛቶች የማረጋጋት ተልዕኮ ከተሰጠው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሰላም አስከባሪ ልዑክ ጋር ይቀላቀላል። “ወታደሮቻችን ቀጣይ ግዴታቸውን ለመወጣት ተዘጋጅተዋል። ተልእኮውን በብቃት ለመወጣት ጥብቅ ስልጠና ወስደዋል እንዲሁም አስፈላጊ ክህሎቶችን ታጥቀዋል። በዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን የበኩላችንን አስተዋጽኦ ለማበርከት ቁርጠኛ ነን" ሲሉ የኬንያ ሰላም አስከባሪ ኃይል አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል ሲሞን ሴዳ ተናግረዋል። እሁድ እለት በሰሜን ኪቩ ግዛት ሉቤሮ ወረዳ በኮንጎ ጦር እና በኤም 23 አማፂ ቡድን መካከል ከባድ ውጊያ በድጋሚ እንደተነሳ ተሰምቷል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ኬንያ የተባበሩት መንግሥታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮን ለመደገፍ ወታደሮቿን ወደ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ አሰማራች
ኬንያ የተባበሩት መንግሥታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮን ለመደገፍ ወታደሮቿን ወደ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ አሰማራች
Sputnik አፍሪካ
ኬንያ የተባበሩት መንግሥታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮን ለመደገፍ ወታደሮቿን ወደ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ አሰማራች የኬንያ ፈጣን ምላሽ ኃይል (KENQRF 4) አራተኛው ክፍለ ጦር የመጀመርያው ቡድን ወደ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ አቅንቷል።... 27.08.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-08-27T10:14+0300
2024-08-27T10:14+0300
2024-08-27T10:46+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
ኬንያ የተባበሩት መንግሥታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮን ለመደገፍ ወታደሮቿን ወደ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ አሰማራች
10:14 27.08.2024 (የተሻሻለ: 10:46 27.08.2024)
ሰብስክራይብ