ኢትዮጵያ አዲስ የወጪ ንግድ ቋሚ ኤግዚቢሽን ማዕከልና ለ5 ቀን የሚቆይ የንግድ ሳምንት ከፈተች አዲስ አበባ ውስጥ በተከፈተው አዲሱ የወጪ ንግድ ኤግዚቢሽን ማዕከል የመክፈቻ ስነ-ስርዓት ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤው እና የገንዘብ ሚኒስትሩን ጨምሮ የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተገኝተዋል። በዝግጅቱ የማዕከሉ እና የኤግዚቢሽኑ ጉብኝት ተካሂዷል። የኢትዮጵያን የወጪ ንግድ ብዝሃነት ለማሳየት የተነደፈው አዲሱ የ730 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው ቋሚ የኤግዚቢሽን ማዕከል የኢትዮጵያን ምርቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ ያለመ ነው። የንግድ ሳምንቱ የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ገዢዎች የንግድ እድሎችን የሚፈልጉበት እና የንግድ ግንኙነቶችን የሚያጠናክሩበት መድረክ እንደሚሆን ይጠበቃል። የንግድ ኤግዚቢሽኑ የፓናል ውይይቶችን እና ለላቀ የንግድ ስራ ውጤቶችና በወጪ ንግድ ዘርፍ ውይይት ላነቃቁ እውቅና የሚሰጥበት የሽልማት ስነ-ስርዓት እንደሚያካትት ታውቋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ኢትዮጵያ አዲስ የወጪ ንግድ ቋሚ ኤግዚቢሽን ማዕከልና ለ5 ቀን የሚቆይ የንግድ ሳምንት ከፈተች
ኢትዮጵያ አዲስ የወጪ ንግድ ቋሚ ኤግዚቢሽን ማዕከልና ለ5 ቀን የሚቆይ የንግድ ሳምንት ከፈተች
Sputnik አፍሪካ
ኢትዮጵያ አዲስ የወጪ ንግድ ቋሚ ኤግዚቢሽን ማዕከልና ለ5 ቀን የሚቆይ የንግድ ሳምንት ከፈተች አዲስ አበባ ውስጥ በተከፈተው አዲሱ የወጪ ንግድ ኤግዚቢሽን ማዕከል የመክፈቻ ስነ-ስርዓት ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤው... 25.08.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-08-25T18:54+0300
2024-08-25T18:54+0300
2024-08-25T19:23+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
ኢትዮጵያ አዲስ የወጪ ንግድ ቋሚ ኤግዚቢሽን ማዕከልና ለ5 ቀን የሚቆይ የንግድ ሳምንት ከፈተች
18:54 25.08.2024 (የተሻሻለ: 19:23 25.08.2024)
ሰብስክራይብ