ኒጀር የህክምና ክፍያን ወጪን በግማሽ ቀነሰች

ሰብስክራይብ
ኒጀር የህክምና ክፍያን ወጪን በግማሽ ቀነሰችእ.አ.አ ነሀሴ  22 ይፋ የሆነው ይህ ማሻሻያ የህብረተሰብ ጤና ተቋማትን ይነካል። እ.አ.አ ከመስከረም 1 ጀምሮ ለማማከር፣ ሆስፒታል ተኝቶ ለመታከም እና ለምርመራ የሚከፈሉ ክፍያዎች በግማሽ ይቀንሳሉ። ከሌሎቹም እፎይታዎች መካከል፡-  የወሊድ አገልግሎት ከክፍያ ነፃ ይሆናል ለኩላሊት እጥበት ይወጣ የነበረው 150,000 የሲ ኤፍ ኤ ፍራንክ (256 ዶላር) ቀርቶ እስከ ህልፈተ ህይወት ድረስ የኩላሊት እጥበት በነጻ ይሰጣል።መንግስት ይህንን ውሳኔ ያሳለፈው በገጠር የሚኖሩ ዜጎች ያላቸው የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ውስን በመሆኑ የማህበራዊ ፍትህን ለማስፈን እና ህብረተሰቡ ወደ ህክምና ተቋማት እንዲመጣ ለማበረታታት እንደሆነ ተነግሯል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0