ኢትዮጵያ የሩሲያ ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ ዘርፍ እንዲሰማሩ እንደምትፈልግ ተናግራለች

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የሩሲያ ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ ዘርፍ እንዲሰማሩ እንደምትፈልግ ተናግራለችየኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ ፍስሃ ይታገሱ በሩሲያ የኢትዮጵያ ኢምባሲ የሚሲዮን ምክትል ኃላፊ ከሆኑት ከሮዛ የሩቅነህ ጋር በቨርቹዋል ውይይት ማድረጋቸው ተዘግቧል። በውይይቱም ሩሲያ በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ውስጥ ያለውን ተሳትፎ ለማስፋት ዕድል መኖሩን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። "ይህንን ግብ ለማሳካት ከኤምባሲያችን ጋር በቅርበት ለመስራት ቁርጠኞች ነን" ሲሉ አቶ ይታገሱ መናገራቸውን የኢትዮጲያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ዘግቧል።አቶ የሩቅነህ በበኩላቸው በኢትዮጵያና በሩሲያ መካከል ያለውን ታሪካዊ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ጠቅሰው፣ የሩሲያ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ለመሰማራት ከፍተኛ ፍላጎት እያሳዩ መሆናቸውንም ገልጸዋል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0