የምስራቅ አፍሪካ የእንስሳት እርባታ እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን እንዲቋቋሙ ያስችላል የተባለ አዲስ ፕሮግራም ይፋ ተደረገ

ሰብስክራይብ
የምስራቅ አፍሪካ የእንስሳት እርባታ እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥን እንዲቋቋሙ ያስችላል የተባለ አዲስ ፕሮግራም ይፋ ተደረገ የኢትዮጵያ የግብርና ሚኒስቴር እና የተመድ የምግብ እና ግብርና ድርጅት (ፋኦ) የአየር ንብረት ለውጥ ተፅእኖን ለመቀነስ እና ለመቆጣጠር ያለመ አህጉራዊ ፕሮግራም ተፈራርመዋል። ፕሮግራሙ በአራት ድንበር ተሻጋሪ ክልሎች ማለትም ማንዴራ፣ ካራሞጃ፣ ማራ-ሴሬንጌቲ እና ባህር አል አረብ - ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳን፣ ታንዛኒያ እና ኡጋንዳን አካቶ ተግባራዊ ይሆናል። ፕሮግራሙ ከፋኦ ምርት፣ ስነ-ምግብ፣ አካባቢ እና ህይወትን የማሻሻል ግብ ጋር ይጣጣማል ተብሏል። ፕሮግራሙ አርብቶ አደር የማህበረሰብ ክፍሎች ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን የበለጠ እንዲቋቋሙ  ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0