የነሐሴ 14 ረፋድ ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፦ 🟠 የናይጄሪያ ባለስልጣናት በኤምፖክስ ስርጭት ምክንያት ከፍተኛውን የስጋት ደረጃ እንዳወጁ አፍሪካ24 የቴሌቭዥን ጣቢያ ዘግቧል። 🟠 የመጀመሪያ ዙር የኤምፖክስ ክትባት በዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ በመጪው ሳምንታት እንደሚደርስ የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር ሳሙኤል ሮጀር ካምባ አስታውቀዋል። 🟠 በአፍሪካ አህጉር የወባ እና የዴንጊ ትኩሳትን ጨምሮ በወባ ትንኝ የሚተላለፉ በሽታዎች እየጨመሩ መምጣታቸውን ከዓለም የወባ ትንኝ ቀን አስቀድመው ሳይንቲስቶች አስጠንቅቀዋል። 🟠 የሴኔጋል ጠቅላይ ሚኒስትር የነዳጅ እና ጋዝ ውሎችን የሚገመግም እና ከብሔራዊ ጥቅም ጋር እንዲጣጣም ሃላፊነት የተጣለበት የህግ፣ ታክስ እና ኢነርጂ ባለሙያዎች ኮሚሽን ማቋቋማቸውን አስታውቀዋል። 🟠 ሁለት የዩክሬን ድሮኖች ክሬሚያ ላይ በአንድ ሌሊት እንደወደሙ የመከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል። 🟠 በክሮከስ አዳራሽ የሽብር ጥቃት ፈጽመዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎች የእስር ጊዜያቸው እስከ ፈረንጆቹ ህዳር 22 እንዲራዘም በተላለፈው ውሳኔ ላይ ይግባኝ ሳይጠይቁ ቀርተዋል። 🟠 ትራምፕ በምርጫ አሸናፊ የሚሆኑ ከሆነ ኤለን መስክ አማካሪ ሆኖ ማየት እንደሚፈልጉ ተናግረዋል። 🟠 ካማላ ሃሪስ በፎክስ ኒውስ የክርክር መድረክ ለመሳተፍ ፈቃደኛ ሳይሆኑ እንደቀሩ ትራምፕ ገለጹ። 🟠 የእስራኤል ጦር በሊባኖስ የሂዝቦላህ የሮኬት ክፍል ቁልፍ አባል የሆነውን ሁሴን አሊ ሁሴንን እንደገደለ አስታወቀ። 🟠 እስራኤል ሀማስ ዋሻዎችን እንዳይቆፍር ለመከላከል በጋዛ ሰርጥ እና ግብፅ መካከል ግንብ በመገንባት እቅዷ እንደጸናች እና በአከባቢው የሚገኙ ካሜራዎችን ልትቆጣጠር እንደሚገባ መግለጿን የአረብ አደራዳሪዎችን ጠቅሰው መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የነሐሴ 14 ረፋድ ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፦
የነሐሴ 14 ረፋድ ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፦
Sputnik አፍሪካ
የነሐሴ 14 ረፋድ ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፦ 🟠 የናይጄሪያ ባለስልጣናት በኤምፖክስ ስርጭት ምክንያት ከፍተኛውን የስጋት ደረጃ እንዳወጁ አፍሪካ24 የቴሌቭዥን ጣቢያ ዘግቧል። 🟠 የመጀመሪያ ዙር የኤምፖክስ ክትባት በዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ በመጪው... 20.08.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-08-20T12:51+0300
2024-08-20T12:51+0300
2024-08-20T13:23+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий