የሳድክ መሪዎች የሻሾ ሰዎችን መብት የሚያስጠብቅ መግለጫ በሙሉ ድምፅ አጸደቁ በዚምባብዌ ሃራሬ በተካሄደው 44ኛው የሳድክ መደበኛ ጉባኤ የደቡብ አፍሪካ ልማት ማህበረሰብ አባል ሀገራት መሪዎች ፈርመው ያጸደቁት መግለጫ በቀጠናው የሚገኙ ሻሾ ሰዎች የሚገጥማቸውን የተለያዩ ችግሮች ለመፍታት ያለመ ነው። “የመሪዎች ጉባኤው የሻሾ ሰዎች ጥበቃ መግለጫን ማጽደቅ እና መፈረሙ የሳድክ አባል ሀገራት ሻሾ ሰዎች የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች ለመፍታት በክልላዊ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ አስፈላጊ እርምጃዎችን ለመውሰድ የጋራ ቁርጠኝነታቸውን የሚያመለክት ነው" ሲል የጉባዔው መግለጫ አስነብቧል። በቀጠናው ሻሾነት ያለባቸው ግለሰቦች ሰፊ መገለልና መድልዎ፣ የጤና እና የትምህርት ተደራሽነት ውስንነት እና ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መገለል ከሚያጋጥሟቸው ፈተናዎች ውስጥ ይካተታሉ። ሳድክ በሻሾ ሰዎች ላይ የሚደረጉ ጥቃቶች እና በደሎችን በተከታታይ ያወግዝ የነበረ ሲሆን ያጸደቀው መግለጫ የእነዚህን ሰዎች ሰብዓዊ መብት ለማስጠበቅ ቁርጠኝነቱን ያሳየ ነው ተብሏል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የሳድክ መሪዎች የሻሾ ሰዎችን መብት የሚያስጠብቅ መግለጫ በሙሉ ድምፅ አጸደቁ
የሳድክ መሪዎች የሻሾ ሰዎችን መብት የሚያስጠብቅ መግለጫ በሙሉ ድምፅ አጸደቁ
Sputnik አፍሪካ
የሳድክ መሪዎች የሻሾ ሰዎችን መብት የሚያስጠብቅ መግለጫ በሙሉ ድምፅ አጸደቁ በዚምባብዌ ሃራሬ በተካሄደው 44ኛው የሳድክ መደበኛ ጉባኤ የደቡብ አፍሪካ ልማት ማህበረሰብ አባል ሀገራት መሪዎች ፈርመው ያጸደቁት መግለጫ በቀጠናው የሚገኙ ሻሾ ሰዎች... 19.08.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-08-19T14:27+0300
2024-08-19T14:27+0300
2024-08-19T14:46+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий