በኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮች ውስጥ የምትገኘው ኢኳቶሪያል ጊኒ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሾመች ፕሬዝዳንት ቴዎዶሮ ኦቢያንግ ንጉዌማ ምባሶጎ ለማኑዌል ኦሳ ንሱዊ የሰጡት የጠቅላይ ሚኒስትርነት ሹመት "ውጤታማ አይደለም" ያሉት የቀድሞው መንግሥት የስራ መልቀቂያ ካስገባ ሶስት ሳምንታት በኋላ የመጣ ነው። ቦታውን በመያዝ የመጀመሪዋ ሴት የነበሩት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ማኑዌላ ሮካ ቦቴይ በፕሬዝዳንቱ ጥያቄ መሰረት ከተሾሙ 18 ወር በኋላ የስራ መልቀቂያቸውን በሐምሌ ወር አስገብተዋል። ምባሶጎ የስራ መልቀቂያው መንግሥት እንደ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ ግኑኝነት እና ሙስና ያሉ ወሳኝ ጉዳዮችን መፍታት ባለመቻሉ የመጣ እንደሆነ ተናግረዋል። አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር እ.አ.አ ከ2012 ጀምሮ የኢኳቶሪያል ጊኒ ብሔራዊ ባንክ ዳይሬክተር በመሆን አገልግለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሀገሪቱን "አስተዳደር የማስተባበር" ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
በኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮች ውስጥ የምትገኘው ኢኳቶሪያል ጊኒ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሾመች
በኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮች ውስጥ የምትገኘው ኢኳቶሪያል ጊኒ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሾመች
Sputnik አፍሪካ
በኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮች ውስጥ የምትገኘው ኢኳቶሪያል ጊኒ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሾመች ፕሬዝዳንት ቴዎዶሮ ኦቢያንግ ንጉዌማ ምባሶጎ ለማኑዌል ኦሳ ንሱዊ የሰጡት የጠቅላይ ሚኒስትርነት ሹመት "ውጤታማ አይደለም" ያሉት የቀድሞው መንግሥት... 17.08.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-08-17T17:01+0300
2024-08-17T17:01+0300
2024-08-17T17:46+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
በኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮች ውስጥ የምትገኘው ኢኳቶሪያል ጊኒ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሾመች
17:01 17.08.2024 (የተሻሻለ: 17:46 17.08.2024)
ሰብስክራይብ