የናይጄሪያ ጦር በ 27 ህገ ወጥ የነዳጅ ማጣሪያዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን እና 100,000 ሊትር የተሰረቀ ድፍድፍ ነዳጅ መያዙን አስታወቀ

ሰብስክራይብ
የናይጄሪያ ጦር በ 27 ህገ ወጥ የነዳጅ ማጣሪያዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን እና 100,000 ሊትር የተሰረቀ ድፍድፍ ነዳጅ መያዙን አስታወቀይህ በኒጀር ወንዝ ዴልታ የተካሄደው ዘመቻ የሀገሪቱን የኢነርጂ ዘርፍ የሚጎዱ ህገወጥ ድርጊቶችን ለመዋጋት የሚደረገውን ጥረት አጉልቶ ያሳያል ሲሉ የጦሩ ቃል አቀባይ ዳንጁማ ዮናስ ዳንጁማ ተናግረዋል። "የ29 ሻለቃ ጦር ነውጠኞች በሚበዙበት እና የህገ ወጦች መናገሻ በሆነው የኢሞ ወንዝ አካባቢ ከ23 በላይ አዲስ የተቋቋሙ ህገ-ወጥ የነዳጅ ማጣራት ቦታዎችን አውድመዋል። ይህ ከ 80,000 ሊትር በላይ የተሰረቀ ድፍድፍ ከያዙ 2 የማከማቻ ማጠራቀሚያዎች በተጨማሪ እንደሆነ  በመግለጫው ተገልጿል።መጠነ ሰፊ የዘይት ስርቆት እና ከነዳጅ ዘይት ማስተላለያ ቧንቧ ላይ ያለው አሻጥር የናይጄሪያን የነዳጅ ምርት በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነስ ወደ ውጭ የሚላከው ምርት ላይ ተፅእኖ በመፍጠር የመንግስትን ፋይናንስ እያሽመደመደው ነው። እነዚህ ጉዳዮች ለፕሬዚዳንት ቦላ ቲኒዩ ሀገር የማረጋጋት ሥራን ትልቅ ፈተና ውስጥ ደቅኗል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0