ዘሌንስኪ በሩሲያ ኩርስክ ክልል ለደርሰው ጥቃት ኃላፊነቱን ወሰዱ

ሰብስክራይብ
ዘሌንስኪ በሩሲያ ኩርስክ ክልል ለደርሰው ጥቃት ኃላፊነቱን ወሰዱ"እንደ ዩክሬን ጦር ዋና አዛዥ ኦሌክሳንደር ሲርስኪ ያሉ በጣም አስፈላጊ ከሆኑ ባልደረቦቼ ጋር  ተገናኝተን በጦር ግንባር ስላለው የመከላከል እርምጃ እና በኩርስክ ክልል ውስጥ ስላደረግነው እንቅስቃሴ ተነግረናል" ሲሉ ዘሌንስኪ በ ኤክስ ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።አክለውም በሩሲያ ግዛት ውስጥ " ለሚከናወነው ዘመቻ" የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የዩክሬን የደህንነት አገልግሎት "የሰብአዊ እቅድ" እንዲያዘጋጁ መመሪያ መስጠታቸውን ተናግረዋል። ባለፈው ሳምንት የዩክሬን ጦር ወደ ሩሲያ ድንበር ጥሶ በኩርስክ ክልል ጥቃት ፈጽሟል። የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጥቃቱ ዙሪያ አስተያየታቸውን ሲሰጡ ዩክሬን ሌላ መጠነ ሰፊ የሆነ ትንኮሳ በማድረግ ንፁሃን ዜጎችን ያለልዩነት ኢላማ አድርጋ ጥቃት መፈፀሟ ተናግረዋል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0