ሰርቢያ ብሪክስን እንደ ጥሩ ዕድል እንደምትመለከት እና የአውሮፓ ህብረት ትክክለኛ አማራጭ እንደሆነ የሀገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተናገሩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አሌክሳንደር ቩሊን ብሪክስ ከሰርቢያ የሚፈልገው አንዳች ነገር እንደሌለ እና ከሚጠየቀው በላይ የሚሰጠው ብዙ እንደሆነ ተናግረዋል። "ይህ ድርጅት ከሰርቢያ የሚጠይቀው ምንም ነገር የለም፡፡ ነገር ግን እኛ ከምንፈልገው በላይ መስጠት ይችላል፡፡ የአውሮፓ ህብረት ከእኛ ሁሉኑም ነገር ይፈልጋል። ይሁንና ህብረቱ ስለሚፈይድልን ነገር እርግጠኛ አይደለሁም። ብሪክስ እድላችንና ትክክለኛው አማራጫችን ነው፡፡ እኔ ሰርቢያ ሁሉኑም የብሪክስ አማራጮች እንድትመለከት እና ከድርጅቱ አባል ሀገራት ጋር የተቀራረበ ትብብር እንድትፈጥር እመርጣለሁ" ሲሉ ከስፑትኒክ ጋር በነበራቸው ቆይታ አብራተዋል፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም የሰርቢያ ባለስልጣናት በሩሲያ ካዛን ለሚካሄደው 14ኛው የብሪክስ ጉባኤ ኦፊሴላዊ ጥሪ በቀጣይ ቀናት ይደርሳቸዋል ብለው እንደሚጠብቁ ገልጸዋል። የብሪክስ ዓመታዊ ጉባኤ እ.አ.አ ከኦክቶበር 22 እስከ 24 በካዛን ይካሄዳል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ሰርቢያ ብሪክስን እንደ ጥሩ ዕድል እንደምትመለከት እና የአውሮፓ ህብረት ትክክለኛ አማራጭ እንደሆነ የሀገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተናገሩ
ሰርቢያ ብሪክስን እንደ ጥሩ ዕድል እንደምትመለከት እና የአውሮፓ ህብረት ትክክለኛ አማራጭ እንደሆነ የሀገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተናገሩ
Sputnik አፍሪካ
ሰርቢያ ብሪክስን እንደ ጥሩ ዕድል እንደምትመለከት እና የአውሮፓ ህብረት ትክክለኛ አማራጭ እንደሆነ የሀገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተናገሩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አሌክሳንደር ቩሊን ብሪክስ ከሰርቢያ የሚፈልገው አንዳች ነገር እንደሌለ እና... 12.08.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-08-12T19:57+0300
2024-08-12T19:57+0300
2024-08-12T20:23+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
ሰርቢያ ብሪክስን እንደ ጥሩ ዕድል እንደምትመለከት እና የአውሮፓ ህብረት ትክክለኛ አማራጭ እንደሆነ የሀገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተናገሩ
19:57 12.08.2024 (የተሻሻለ: 20:23 12.08.2024)
ሰብስክራይብ